Saturday, 27 June 2015 08:14

ኢትዮጵያውያን አሜሪካን በመውደድ ከአለም 3ኛ ተብለዋል

Written by 
Rate this item
(5 votes)

- የፊሊፒንሳውያንን ያህል አሜሪካን የሚወድ የለም
- አሜሪካን በመጥላት የዮርዳኖስ ህዝቦች ይመራሉ

አሜሪካን በተመለከተ ያላቸውን አመላካት ለመለካከት ታስቦ በ39 የተለያዩ የዓለማችን አገራት ላይ የተሰራ አንድ ጥናት፣ ኢትዮጵያውያን አሜሪካን በመውደድ 3ኛ ደረጃ እንደያዙ መረጋገጡን ዘ ቢዝነስ ኢንሳይደር ዘገበ፡፡ፒው ሪሰርች ሴንተር የተባለው የምርምር ተቋም በሰራው በዚህ ጥናት፣ አሜሪካን አጥብቀው
በመውደድ ቀዳሚዎቹ የፊሊፒንስ ዜጎች ሲሆኑ፣ ጋናውያንና ኢትዮጵያውያን ይከተላሉ ብሏል፡፡በጥናቱ ከተካተቱ ፊሊፒንሳውያን መካከል 85 በመቶው አሜሪካን እንደሚወዱ ሲናገሩ፣ በጋና 83 በመቶ፣ በኢትዮጵያ ደግሞ 75 በመቶ የሚሆነው ህዝብ ለአሜሪካ ፍቅር እንዳለው ለማወቅ ተችሏል፡፡አሜሪካን በመውደድ ከሰሃራ በታች ያሉ የአፍሪካ አገራት ህዝቦች ቀዳሚውን ስፍራ እንደሚይዙ የጠቆመው ጥናቱ፣ አብዛኞቹ የአውሮፓ፣ የእስያና የላቲን አሜሪካ አገራት ህዝቦችም ለአሜሪካ በጎ አመለካከት እንዳላቸው ማረጋገጡን ጠቁሟል፡፡
በአንጻሩ ደግሞ አሜሪካን በመጥላት የዮርዳኖስ ህዝቦች ቀዳሚ ሆነው ተገኝተዋል፡፡ በጥናቱ ከተካተቱ የአገሪቱ ዜጎች 83 በመቶ ያህሉ አሜሪካን እንደማይወዱ ተናግረዋል፡፡ በሁለተኛ ደረጃ አሜሪካን የሚጠሉት ደግሞ ሩስያውያን ሲሆኑ በተለይ  ከቅርብ አመታት ወዲህ አሜሪካን የሚጠሉ ሩስያውያን ቁጥር እየጨመረ መምጣቱንም ጥናቱ አረጋግጧል፡፡

Read 4500 times