Saturday, 20 June 2015 12:19

-ለ“የኛ” የሚሰጠው የ16 ሚ. ፓውንድ የገንዘብ ድጋፍ ተቃውሞ ገጠመው

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

 ዲፊድ ፕሮጀክቱ ተጽዕኖ ፈጣሪ መሆኑ በመረጋገጡድጋፍ ይገባዋል ብሏል

    የእንግሊዝ አለም አቀፍ የልማት ድርጅት (ዲፊድ)በኢትዮጵያ የልጃገረዶችን አቅም ለመገንባት ታስቦ
ተግባራዊ በመደረግ ላይ ለሚገኘው “የኛ” ፕሮጀክትሁለተኛ ምዕራፍ ማስፈጸሚያ ሊሰጠው ያሰበው
ተጨማሪ የ16 ሚሊዮን ፓውንድ የገንዘብ ድጋፍተቃውሞ እንደገጠመው ዴይሊ ሜይል ዘገበ፡፡ገንዘቡን የሚረዳው ዲፊድ በበኩሉ፤ በፕሮጀክቱ ላይባደረገው ግምገማ አዎንታዊ ተጽዕኖ እያሳደረና ተጨማሪልጃገረዶች ትምህርታቸውን እንዲቀጥሉ እያበረታታቸውመሆኑን የሚያሳዩ ውጤቶች ማግኘቱን ገልጾ፣ ገንዘቡመሰጠቱና ፕሮጀክቱ በቀጣይነት መደገፉ አግባብነትአለው ብሏል፡፡ዲፊድ 54 ሚሊዮን የእንግሊዝ ፓውንድለተመደበለት የገርል ሃብ ፕሮጀክት ሁለተኛ ምዕራፍማስፈጸሚያ የሚውል ተጨማሪ 16 ሚሊዮን ፓውንድለመስጠት መወሰኑን በይፋ ለመግለጽ በዝግጅትላይ መሆኑን የጠቆመው ዴይሊ ሜይል፤ የእርዳታተጽዕኖዎችን የሚያጠና አንድ የአገሪቱ ገለልተኛኮሚሽን ግን፣ የፕሮጀክቱ የስራ ሃላፊዎች የፕሮጀክቱንውጤታማነት በተጨባጭ ማሳየት እስካልቻሉ ድረስየገንዘብ ድጋፉን እንዲያቋርጡ ለሚመለከታቸውሚንስትሮች ማስጠንቀቂያ ሰጥቷል ብሏል፡፡ገለልተኛ ኮሚሽኑ ከትናንት በስቲያ ያወጣውንሪፖርት ጠቅሶ ዴይሊ ሜይል እንደዘገበው፤ ዲፊድ የገርልሃብን ውጤታማነት ሚያረጋግጥና ተጨማሪ የገንዘብድጋፍ ለማድረግ የሚያስወስነው ከገለልተኛ አካል የተገኘማስረጃ የለውም ብሏል፡፡ፕሮጀክቱ በናይጀሪያ በተለያዩ ምክንያቶች ውጤታማአለመሆኑ በሁሉም አካላት ዘንድ መታመኑን የገለጸውሪፖርቱ፣ በ ኢትዮጵያ ወ ይም በ ሩዋንዳም የ ፕሮጀክቱን ውጤታማነት በተመለከተ የሚቀርቡ ማስረጃዎችአስተማማኝ አይደሉም ብሏል፡፡የእንግሊዝ የግብርከፋዮች ማህበር ዋና ስራ አስፈጻሚ ጆናታን አይሳቢበበኩላቸው፣
የእንግሊዝ ባለስልጣናት ተገቢነታቸውአጠያያቂ በሆኑ የሌሎች አገራት ፕሮጀክቶች ላይይሄን ያህል ከፍተኛ ገንዘብ እንዲባክን መተባበራቸው፣የአገሪቱን ግብር ከፋዮች እጅግ የሚያስደነግጥ አስገራሚጉዳይ ነው ማለታቸውን ዘገባው ገልጿል፡፡ ገርል ሃብከናይኪ ፋውንዴሽን ጋር በጥምረት የሚተገበር መሆኑንና
እስካሁንም ከእንግሊዝ ግብር ከፋዮች የተሰበሰበ 27.1ሚሊዮን ፓውንድ በድጋፍ ማግኘቱን ስታወሰውሪፖርቱ፣ የፕሮጀክቱ አስተዳደር እንደሚያሳስበው ጠቅሶ፣ናይኪ ሃላፊነቱን በአግባቡ መወጣቱም አጠያያቂ ነውብሏል፡፡ የፕሮጀክቱ ቃል አቀባይ በበኩላቸው፤ ፕሮጀክቱየአፍሪካውያን ልጃገረዶችን ህይወት ለማሻሻል ታስቦመተግበር ከጀመረበት እ.ኤ.አ 2010 ጀምሮ፣ በሚሊዮኖችየሚቆጠሩ በድህነት ውስጥ የሚኖሩ ልጃገረዶችን፣ ወጣትወንዶችንና አዋቂዎችን ተጠቃሚ ያደረጉ የማህበራዊናየግንዛቤ ለውጥ ስራዎችን አከናውነናል ብለዋል፡፡“ለአብነትም በኢትዮጵያ በመተላለፍ ላይ የሚገኘውንየኛ የሬዲዮ ድራማና ቶክ ሾው ከሚከታተሉ ልጃገረዶች መካከል 84 በመቶው በራስ መተማመናቸውንለማሳደግ እንደረዳቸው ማረጋገጣቸውንና 76 በመቶየሚሆኑትም ትምህርታቸውን እንዲቀጥሉ እንዳነሳሳቸውመመስከራቸውን መጥቀስ ይቻላል” ብለዋል ቃል

Read 2741 times