በደራሲ ተወልደ ሲሳይ የተፃፈው “77” የተሰኘው በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተመሰረተ ልብወለድ መፅሃፍ ሰሞኑን ለገበያ ቀረበ፡፡ መፅሃፉ መቼቱን በ1977 በኢትዮጵያ በተከሰተውና በመቶ ሺ የሚቆጠሩ ዜጎችን በፈጀው ድርቅና ረሃብ ላይ ያደረገ ነው ተብሏል፡፡
ደራሲው የመፅሃፉን መታሰቢያነት በ1977 ድርቅና መከራ ምክንያት ህይወታቸው ላለፈ፣ ህይወት ለተመሰቃቀለባቸውና በአጠቃላይ የወቅቱ ሰለባ ለሆኑ ኢትዮጵያውያን አድርጓል፡፡ በ 363 ገፆች የተቀነበበው መጽሐፉ፤ ለአገር ውስጥ በ75 ብር፣ ለውጭ አገር በ20 ዶላር እንደሚሸጥ ታውቋል፡፡