Saturday, 20 June 2015 11:44

“77” መፅሐፍ ለገበያ ቀረበ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

  በደራሲ ተወልደ ሲሳይ የተፃፈው “77” የተሰኘው በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተመሰረተ ልብወለድ መፅሃፍ ሰሞኑን ለገበያ ቀረበ፡፡ መፅሃፉ መቼቱን በ1977 በኢትዮጵያ በተከሰተውና በመቶ ሺ የሚቆጠሩ ዜጎችን በፈጀው ድርቅና ረሃብ ላይ ያደረገ ነው ተብሏል፡፡
ደራሲው የመፅሃፉን መታሰቢያነት በ1977 ድርቅና መከራ ምክንያት ህይወታቸው ላለፈ፣ ህይወት ለተመሰቃቀለባቸውና በአጠቃላይ የወቅቱ ሰለባ ለሆኑ ኢትዮጵያውያን አድርጓል፡፡ በ 363 ገፆች የተቀነበበው መጽሐፉ፤ ለአገር ውስጥ በ75 ብር፣ ለውጭ አገር በ20 ዶላር እንደሚሸጥ ታውቋል፡፡

Read 1750 times