Saturday, 20 June 2015 11:42

“ሁለት ገፅ” ልቦለድ ለንባብ በቃ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

 በደራሲ እያዩ ደባስ የተፃፈው “ሁለት ገፅ” የተሰኘ ረዥም ልቦለድ መፅሃፍ ሰሞኑን ለንባብ በቃ፡፡ ደራሲው በመግቢያው ላይ ባሰፈረው መልዕክት፤ “ተረጋጉ፤ አትረበሹ፤ አትጨነቁ፡፡ ስለማንም ቢሆን ክፉ አታስቡ፡፡ መልካምነት ከጉያችሁ ስር ያለ ቅርባችሁ ነው፡፡ በእናንተ ውስጥ ትልቅ ኃይልና መሰጠት አለ፡፡ ያንን ፈልጉ፡፡ ሰዎችን አትመልከቱ፡፡ ራሳችሁን እዩ…” እያለ ይቀጥላል፡፡
በ171 ገፆች ተሰናድቶ የቀረበው መፅሃፉ፤ በማራኪ የታሪክ ፍሰትና አወቃቀር ተሰናስሎ የቀረበ መሆኑን ደራሲው ጠቁሟል፡፡ ከሚቀጥሉት ሥራዎቹ ቀዳሚ ያላቸውንም “የሶርዲኒያሞቹ ምዛዥ”፣ “ቤንዚኒስ” እና “አሽዶዳውያን” በሚል ጠቅሷል፡፡

Read 1941 times