“ግጥም ሙዚቃና ስዕል፤ ልዩነትና ተዛምዶ” በሚል ርዕስ በነገው ዕለት በብሔራዊ ቤተ መፅሐፍትና ቤተ መዛግብት ኤጀንሲ አዳራሽ ከቀኑ 8 ሰዓት ተኩል ጀምሮ ውይይት እንደሚካሄድ ሚዩዚክ ሜይዴይ ኢትዮጵያ አስታወቀ፡፡
ለውይይት መነሻ ሃሳብ የሚያቀርበው ገጣሚ ኤፍሬም ስዩም ሲሆን በዝግጅቱ ላይ ገጣሚያን፣ ደራሲያን የሙዚቃ ባለሙያዎችና የጥበብ ቤተሰቦች እንደሚገኙ ተጠቁሟል፡፡
የውይይት ፕሮግራሙን ሚዩዚክ ሜይዴይ ኢትዮጵያ ከኢትዮጲስ ኮሌጅ ጋር በመተባበር ያሰናዳው ሲሆን ከውይይቱ በተጨማሪ የመፃሕፍት ንባብ መርሃ ግብርም የዝግጅቱ አካል እንደሆነ ታውቋል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና