Saturday, 20 June 2015 11:39

የሰዓሊ ግዛቸው ከበደ የስዕል ኤግዚቢሽን ተከፈተ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

የሰዓሊ ግዛቸው ከበደ 20 የሚደርሱ የስዕል ሥራዎች ለዕይታ የሚቀርቡበት ኤግዚቢሽን በትላንትናው ዕለት ምሽት ከገርጂ መብራት ኃይል ወደ ሳሊተ ምህረት በሚወስደው መንገድ፣ ከሮቤራ ካፌ ጀርባ፣ በማላንጋ የስዕል ጋለሪ ተከፈተ፡፡ ኤግዚቢሽኑ ለተመልካች ክፍት የሚሆነው ዘወትር ቅዳሜና እሁድ፣ ለአራት ተከታታይ ሳምንታት ነው ተብሏል፡፡ ሰዓሊው የአሁኑን ጨምሮ በ50 የስዕል ኤግዚቢሽኖች ላይ (በግልና በቡድን) ሥራዎቹን እንዳቀረበ ለማወቅ ተችሏል፡፡ ሰዓሊና ቀራጺ ግዛቸው ከበደ፤ ከዚህ ቀደም ዘመን ባንክ በር ላይ የቆመውንና በአሜሪካ የስቶክ ገበያ ተምሳሌት የሆነውን  የበሬ ኮርማ (bull) ፣ከፊትለፊቱ  በኦዳ ታወር ላይ ያለውን ሞሳይክ መስራቱ የሚታወቅ ሲሆን ስቴዲየም በሚገኘው የኦሮምያ ባህል ማዕከል ባለ ሁለት አውታረ መጠን ቅርጾችንም ሰርቷል፡፡   

Read 1154 times