Saturday, 13 June 2015 14:33

ሲኖማርክ በኢትዮጵያ ትልቁን ሪልስቴት ሊገነባ ነው

Written by 
Rate this item
(10 votes)

በጎተራ የሚገነባው መንደር 4 ቢሊዮን ብር ተመድቦለታል
           ሲኖማርክ የተባለው የሪልስቴት አልሚ ኩባንያ፤ በኢትዮጵያ ትልቁን የመኖሪያ ቤቶች ግንባታ ፕሮጀክት በአዲስ አበባ ሊጀምር መሆኑን አስታወቀ። ኩባንያው በ4 ቢሊዮን ብር ወጪ ጎተራ አካባቢ ሊያስገነባው ያቀደው የሪልስቴት መንደር “ሮያል ጋርደን” የሚል ስያሜ ያለው ሲሆን፣ እያንዳንዳቸው 20 ወለሎች ያሏቸው 14 ህንፃዎች እንደሚኖሩት የኩባንያው ማርኬቲንግ ማኔጀር አቶ ተስፋዬ ገ/የሱስ ተናግረዋል፡፡
ጥራታቸውን የጠበቁ ዘመናዊ መኖሪያ ቤቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለኢትዮጵያውያን የማቅረብ አላማ
እንዳለው የገለጸው ኩባንያው፣ የሪልስቴት መንደሩ የመዋኛ ገንዳዎች፣ የህፃናት መጫወቻዎች፣ የስፖርት ማዘውተሪያ ማዕከላትና የንግድ ዞን እንደሚኖረውና አገር በቀሉ ሳባ ኢንጂነሪንግ በግንባታው ንደሚሳተፍበት አስታውቋል፡፡ሪል እስቴቱ የሚያስገነባቸው ህንፃዎች የየራሳቸው ሁለት ሁለት ሊፍቶች፣ ጀነሬተርና የውሃ ማጣሪያ ማሽኖች የሚኖራቸው ሲሆን የሪልስቴት መንደሩ ግንባታ በሶስት አመት ጊዜ ውስጥ ይጠናቀቃል ተብሎ እንደሚጠበቅም ተጠቁሟል፡፡ የቤቶቹ ዋጋ የፊታችን ሰኞ ይፋ ይደረጋል ተብሏል፡፡ ሲኖማርክ ሪልስቴት ላለፉት 7 አመታት በቻይናና በሌሎች አገራት የተለያዩ ታላላቅ የኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶችን በተሳካ ሁኔታ በማከናወን የሚታወቀው የቻይናው ሲንቹዋን ሄንግያንግ
ኢንቨስትመንት እህት ኩባንያ ነው፡፡

Read 4984 times