Saturday, 06 June 2015 14:30

ሻርፕ ዘንድሮ 1.45 ቢሊዮን ዶላር እንደሚከስር ይጠበቃል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

  ከአለማችን ታላላቅ የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች አምራች ኩባንያዎች ተርታ የሚሰለፈው የጃፓኑ ሻርፕ ኩባንያ፣ በያዝነው የፈረንጆች አመት  ብቻ 1.45 ቢሊዮን ዶላር ይከስራል ተብሎ እንደሚጠበቅ ሮይተርስ ዘገበ፡፡
ከቅርብ አመታት ወዲህ እየደረሰበት ካለው ኪሳራ ለማገገም ደፋ ቀና ማለቱን የቀጠለው ሻርፕ፣ በዘንድሮው አመት  1.45 ቢሊዮን ዶላር ኪሳራ ይደርስበታል ተብሎ እንደሚጠበቅ የጃፓኑ ኮዮዶ ኒውስ ይፋ ያደረገውን መረጃ ጠቅሶ ዘገባው ገልጧል፡፡
ኩባንያው ባለፈው አመት 222 ቢሊዮን የጃፓን የን መክሰሩን ያስታወሰው ዘገባው፣ የአምናው ኪሳራው ባለፉት አራት አመታት ከደረሱበት ኪሳራዎች በሶስተኛ ደረጃ ላይ እንደሚገኝም ገልጧል፡፡ ኩባንያው ባለፉት አመታት ለከፍተኛ ኪሳራ የተዳረገው በተለያዩ አለማቀፋዊና ውስጣዊ ምክንያቶች መሆኑን የጠቆመው ዘገባው፣ ከእነዚህም መካከል የምርቶች ሽያጩ መቀነሱ፣ የገበያ ውድድሩ ከፍተኛ መሆኑና የወጪዎች መብዛት ይጠቀሳሉ ብሏል፡፡ ሻርፕ ባለፈው አመት በአለም ዙሪያ ከሚገኙ 49 ሺህ ሰራተኞቹ መካከል 10 በመቶውን ከስራ እንደቀነሰና ከእነዚህም መካከል 3ሺህ 500 የሚሆኑት በጃፓን ይሰሩ የነበሩ መሆናቸውንም ዘገባው አክሎ ገልጧል፡፡

Read 1733 times