Saturday, 30 May 2015 12:54

ድርጅየኢትዮጵያ ቱሪስት ንግድ ሥራ ት ሁለት ዋንጫዎች ተሸለመ

Written by  መንግሥቱ አበበ
Rate this item
(1 Vote)

 

 

 

50ኛ ዓመት ኢዮቤልዩ በዓሉን አከበረ

 የኢትዮጵያ ቱሪስት ንግድ ሥራ ድርጅት ከፕራይቬታይዜሽንና የመንግስት የልማት ድርጅቶች ተቆጣጣሪ ኤጀንሲ ስር ካሉ የልማት ድርጅቶች መካከል ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ በማስገኘቱና የላቀ ውጤት በማስመዝገቡ የምስጋና የምስክር ወረቀትና ዋንጫ መሸለሙን የድርጅቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ገለጹ፡፡ ዋና ሥራ አስኪያጁ አቶ አሰፋ ጉያ ትናንት በድርጅቱ ጽ/ቤት በሰጡት መግለጫ፣ ድርጅቱ በ2006 ዓ.ም በፕራይቬታይዜሽንና የመንግስት የልማት ድርጅቶች የላቀ ውጤት በማስመዝገብ 12.5 ሚሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሪ በማስገኘቱ መሸለሙን ገልጸዋል፡፡

ቱሪስት ንግድ ሥራ ድርጅት ከኤፕሪል 23-27, 2015 በተደረገው 4ኛው ልዩ ኢንተርናሽናል የቱሪዝም የአስጐብኚ ድርጅት  አውደ ርዕይ የላቀ ተሳትፎ በማበርከቱ ከአዲስ አበባ ንግድና ዘርፍ ማህበራት ም/ቤት ዋንጫና የምስክር ወረቀት መሸለሙን ሥራ አስኪያጁ አስታውቀዋል፡፡ ድርጅቱ የተመሰረተበትን 50ኛ ኢዮቤልዮ ክብረ በዓሉን በተለያዩ ዝግጅቶች ማክበሩንና ለድርጅቱ መስራች ለአቶ ኃ/ሥላሴ ታፈሰና የላቀ የሥራ ውጤት ላስመዘገቡ ሠራተኞች የምስጋና ሽልማት መስጠቱን ገልጸዋል፡፡

 

 

 

 

Read 2059 times