Print this page
Saturday, 30 May 2015 12:34

“የራዕይ እግሮች” ነገ ይመረቃል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

     የገጣሚ ኃይሌ ተስፋዬ ቸኮል የግጥም ስብስቦች የተካተቱበት “የራዕይ እግሮች” የተሰኘ የግጥም መድበል ነገ ከጧቱ 3፡00 ጀምሮ በፍፁም ሲኒማ ይመረቃል፡፡ የግጥሙ ይዘት ማህበራዊ፣ መንፈሳዊና ፖለቲካዊ ትዝብት ላይ የሚያተኩር ሲሆን የግዕዝን ቋንቋ በመቀላቀል በጠንካራ አገላለፅ የታጀበ ነው ተብሏል፡፡

ገጣሚው ግጥም ወደመፃፍ የተሳበበትን ምክንያት በመድበሉ መግቢያ ላይ ሲያስረዳ፤ “ገና በ11 ዓመቴ አካባቢ ቤተክርስቲያን ስማር የእነሙሴን፣ ዳዊትን … ረዣዥም ግጥሞች ከመፅሀፍ ቅዱስ ቃል በቃል እገለብጥ ነበር፡፡ ይህ የህይወት ልምምድም እድሜዬ እየጨመረ በመጣ ጊዜ ትልቅ ዕርዳታ አድርጎልኛል” ብሏል ገጣሚው፡፡ በ110 ገፆች የተቀነበበው መድበሉ፤ 73 ግጥሞችን ያካተተ ሲሆን ለአገር ውስጥ በብር 35.50፣ ለውጭ ደግሞ በ15 ዶላር እንደሚሸጥ ታውቋል፡፡ 

 

Read 1546 times
Administrator

Latest from Administrator