Saturday, 30 May 2015 12:09

የብሩንዲው መሪ ህዝቡ ለምርጫው ገንዘብ እንዲያዋጣ ጠየቁ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 

 

 

     የባንክ ሒሳብ ደብተር ቁጥር ይፋ አድርገዋል

    የአገሪቱ ህገ መንግስት ከሚፈቅድላቸው ውጪ ለሶስተኛ ዙር በምርጫ ለመወዳደር መወሰናቸው ከፍተኛ ተቃውሞና የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ ያደረሰባቸው የብሩንዲው ፕሬዚደንት ፔሪ ንኩሩንዚዛ፣ ህዝቡ ምርጫውን በገንዘብ እንዲደግፍ ጥሪ ማቅረባቸውን ሲኤንኤን ዘገበ፡፡

ከምርጫው ራሳቸውን እንዲያገሉ የሚደርስባቸውን ውስጣዊና ውጫዊ ጫና አልሰማም ብለው ለመወዳደር የቆረጡት ፕሬዚዳንቱ፣ አለማቀፉ ማህበረሰብ ለምርጫው ማስፈጸሚያ ቃል የገባውን የገንዘብ ድጋፍ ላለመስጠት በመወሰኑ ህዝቡ የገንዘብ ድጋፍ እንዲያደርግ በፌስቡክ ገጻቸው ጥሪ አድርገዋል፡፡

“የኔን በምርጫ መወዳደር የደገፍክ የአገሬ ህዝብ ሆይ!... ለምርጫው ስኬታማነት በፈቃድህ የቻልከውን ያህል የገንዘብ ድጋፍ አድርግ” ያሉት ፕሬዚዳንት ኑኩሩንዚዛ፣ ህዝባቸው ለምርጫው የገንዘብ ድጋፍ የሚያደርግበትን የባንክ የሒሳብ ቁጥርም ይፋ አድርገዋል፡፡

የፕሬዚዳንቱ በምርጫ የመወዳደር ውሳኔ ይፋ መደረጉን ተከትሎ በአገሪቱ የተቀሰቀሰው ግጭት ያሰጋቸው ከ100 ሺህ በላይ ዜጎች ወደ ጎረቤት አገራት መሰደዳቸውን ያስታወሰው ዘገባው፣ የተወሰነ መረጋጋት ቢፈጠርም ተቃውሞው እንደቀጠለ መሆኑንና ፕሬዚዳንቱም ምርጫውን በመጪው ሰኔ መጨረሻ ለማካሄድ መወሰናቸውን አክሎ ገልጿል፡፡

 

 

 

Read 1177 times