Print this page
Saturday, 30 May 2015 12:12

ደቡብ ሱዳን በታሪኳ አስከፊ የምግብ እጥረት ገጥሟታል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 

 

 

ከ4.6 ሚሊዮን በላይ ህዝብ አደገኛ ርሃብ ተጋርጦበታል

    የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የምግብ ፕሮግራም፤ ደቡብ ሱዳን በታሪኳ አስከፊ የተባለው የምግብ እጥረት እንደገጠማትና 40 በመቶው የአገሪቱ ህዝብ በመጪዎቹ ጥቂት ወራት አስቸኳይ የምግብ እህል እርዳታ እንደሚያስፈልገው መግለጹን ቢቢሲ ዘገበ፡፡

የእርስ በእርስ ግጭት፣ የምግብ ዋጋ መናርና እየተባባሰ የመጣው የኢኮኖሚ ቀውስ፣ በደቡብ ሱዳን ከፍተኛ የምግብ እጥረት መፍጠሩን ያስታወቀው የአለም የምግብ ፕሮግራም፣ 4.6 ሚሊዮን የሚሆነው የአገሪቱ ህዝብ በመጪዎቹ ሶስት ወራት አስከፊ ርሃብ ላይ ይወድቃል ብሏል፡፡

እያሽቆለቆለ የመጣው የአገሪቱ ኢኮኖሚ ችግሩን በአፋጣኝ ሊያባብሰው እንደሚችል ያለውን ስጋትም ገልጾ፣ አለማቀፉ ማህበረሰብ በአገሪቱ የተከሰተውን የምግብ እጥረት ለመፍታትና ርሃቡ የሚያደርሰውን ጥፋት ለመቀነስ አስቸኳይ የምግብና የነፍስ አድን እርዳታ ማድረግ ይጠበቅበታል ሲልም ጥሪውን አቅርቧል፡፡

የምግብ እጥረቱ በተለይም የመንግስትና የአማጽያን ሃይሎች ተደጋጋሚ ግጭት ሲያደርጉባቸው በቆዩትና በርካታ ዜጎች በተፈናቀሉባቸው በጆንግሊ፣ አፐር ናይልና ኒቲ ግዛቶች የተባባሰ እንደሆነ ከትናንት በስቲያ ብሉምበርግ ዘግቧል፡፡

በአፐር ናይል ግዛት የታየው የግብርና ግብዓቶች እጥረት በምርታማነት ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ ፈጥሯል ያለው የአለም የምግብ ፕሮግራም፣ በዚህም አገሪቱ በዘንድሮው አመት ማምረት ከሚገባት የጥራጥሬ እህል ምርት 249 ሺህ ሜትሪክ ቶን ጉድለት እንዲፈጠር አድርጓል ብሏል ብሉምበርግ፡፡

በደቡብ ሱዳን መንግስትና በአማጽያን መካከል በ2013 የተቀሰቀሰውና ተባብሶ የቀጠለው ግጭት፣ ከ2 ሚሊዮን በላይ የአገሪቱን ዜጎች እንዳፈናቀለም ዘገባው አስታውሷል፡፡

 -

 

 

 

Read 1308 times
Administrator

Latest from Administrator