“የሳጥናኤል ሳል ኢትዮጵያ” የህይወት ዛፍ” “ገነት” “ኢትዮጵያ” የሚል ርዕስ ያለውና በጋዜጠኛና ደራሲ ፍሰሓ ያዜ ካሳ የተጻፈው መጽሃፍ በያዝነው ሳምንት በገበያ ላይ ውሎ እየተሸጠ ይገኛል፡፡ መጽሃፉ የዓለም ሃያላን አገራትና መሪዎቻቸው በህብረት ሆነው በኢትዮጵያ ላይ ያነጣጠሩበትን ምክንያትና ዋነኛ ግባቸውን የሚተነትን ነው ያለው ደራሲው፤ 376 ገጾች እንዳሉትና በ80 ብር እየተሸጠ እንደሚገኝም ለአዲስ አድማስ ተናግሯል፡፡
ጋዜጠኛና ደራሲ ፍሰሐ ያዜ ካሳ ከዚህ ቀደም “የኢትዮጵያ የ5ሺህ ዓመት ታሪክ፣ ከኖህ እስከ ኢህአዴግ”፣ “ካልተዘመረለት እያሱ እስከተዘመረለት ኢህአዴግ” እንዲሁም “እኔና ቹ” የተሰኙ ሦስት መጽሃፍትን ለአንባቢያን አድርሷል፡፡