Tuesday, 26 May 2015 08:39

“ከሚሽግዳ እስከ ዓለም ዳርቻ” ለንባብ በቃ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 

 

 

    የ73ቱ ዓመቱን የዕድሜ ባለፀጋ የዶክተር ተስፋፅዮን ደለለ ግለ-ታሪክ የሚያስነብበው “ከሚሽግዳ እስከ ዓለም ዳርቻ (ሕይወቴ ትምህርት ቤቴ)” የተሰኘ መጽሐፍ ሰሞኑን ለንባብ በቃ፡፡ ግለ-ታሪኩን የፃፉት ራሳቸው ዶ/ር ተስፋጽዮን ሲሆኑ የአርትኦት ሥራውን ያከናወነው ገጣሚ ወንድዬ ዓሊ እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል፡፡

የፖፑሌሽን ሚዲያ ሴንተር የኢትዮጵያ ተጠሪ ዶ/ር ንጉሴ ተፈራ በመጽሐፉ ጀርባ ላይ በሰጡት አስተያየት፤ “ይህ መጽሐፍ እግዚአብሔር በዶ/ር ተስፋፅዮን ህይወት ውስጥ ያደረገውን በጐ ነገር እንድታውቁ የሚረዳችሁ ብቻ ሳይሆን “‹በእኔ የህይወት ጉዞ የታየ ትርጉም ያለው ድርሻ ምንድን ነበር” ብላችሁ እንድትጠይቁ ያደርጋችኋል… ሁሉም ሊያነበው የሚገባ ቁምነገር የያዘ መጽሐፍ” ብለውታል፡፡

የመፅሐፉ አርታዒ ገጣሚ ወንድዬ አሊ በበኩሉ፤ “አተራረኩ ሲበዛ ተፈጥሮአዊ ከመሆኑ የተነሳ የጋሽ ተስፋን ረቂቅ ኩል መኳኳል፣ እንሶስላ ማሞቅ አላስፈለገኝም፤ በርኖስ ላይ ካቦርታ መደረብ ነውና፡፡” ሲል አስተያየቱን ገልጿል፡፡ በ10 ምዕራፎችና በ284 ገፆች የተቀነበበው መጽሐፉ፤ በ80 ብር እየተሸጠ ነው፡፡

   

 

 

 

Read 1381 times