Tuesday, 26 May 2015 08:23

የሚዲያ አብዮት ‹‹ሽምጠጣ እና ፍጥፈጣ››

Written by  ሜርዶቂዮስ
Rate this item
(1 Vote)

 

 

 

   ‹‹አብዮት፤ አበየ ፤እምቢ አለ ከሚለው የግዕዝ ቃል የመጣ ነው›› የሚለው ዬኔታ ስብሀት፤ የመጀመሪያው አብዮተኛ ሰይጣን ዲያቢሎስ ነው ይላል፡፡ በእንግዳና ተቆርቋሪም ‹‹ጋዜጠኛ›› መሳይ አቀራረብ ‹‹በእውኑ እግዚአብሔር ከዚህ በገነት መካከል ከሚገኘው ፍሬ እንዳትበሉ አዝዟልን…›› በሚል ህልውናን ተፈታታኝ ጥያቄ አብዮቱን ያቀጣጠለባቸው ምስኪኖቹ አዳምና ሄዋን ግን ‹‹ሰው›› ነበሩ፡፡ የሰው ልጅ ታሪክ የሚጀምረው ከውድቀት ነው፡፡ ‹‹ሰው አፈር ነው አሉ፤ ሰው አፈር ነወይ…አዬ ሰው አፈር ነወይ…›› ትላለች ሙሾ አውራጅ፡፡ አዎ እናቴ! ያውም ስድስት ክንድ መሬት ውስጥ ኩርምት ብሎ የሚረሳ ነዋ! አስከሬኑም ከሌሎች እንስሳት አንጻር ለመበላሸት ይቸኩላል፡፡ ‹‹የኔ ቢጤው›› ደግሞ ያውም ከስህተቱ የማይማር፤ታጥቦ ጭቃ! እንዴት ማለት መልካም…በዚያው በኦሪት አቀራረብ በሰዎች መካከል ጠብንና አለመተማመንን መዝራት ተለምዶ! ምነው…አይባልም! ነውር ነው! ፋሽን ሁኗላ! እናም በአለም ላይ የመጀመሪያው ቀጣፊና ዋሾ ሰውን አሳተ! ቃየን ተወለደ። ‹‹ያዳቆነ ሰይጣን ሳያቀስስ አይመለስም›› የኦሪት ተረት ነች መሰለኝ፡፡ ሴጣን ዲያቢሎስ ዳግም በቃየን ልብ ቅናት ሆኖ ገብቶ አቤልን አስገደለ!

 ይህን መንገድ ገና በዘፍጥረት በኖሩ ሰዎች ላይ ስናየው ባይገርመንም አሁን ላይ ቆመን አወራረዱ ሰውን ምንኛ ከራሱ ጋር እንዳቆራረጠው ስናስተውል ግን ዘግናኝ ሆኖ ይገኛል፡፡ ማን ነበር ‹‹አላዋቂን ብታስደምም ተመራማሪን ታስቀይማለህ›› ያለው…እህ! ይኸዋ ያንኑ የቀድሞውን የኦሪት አልባስ ‹‹ሰው›› በልኩ እያስጠበበና እያስሰፋ ሲለብሰው ይኖራል፡፡ ታላቁ እስክንድር የአምላከ አማልእክቱ የዜዩስ ልጅ ነኝ፡ ፈረሴም እንዲሁ! አለ። ሸመጠጠ፡፡ በአፍ የተናፈሰ ገድሉ ገና በሩቁ የሰሙትን ሁሉ እያርበደበደ አለምን በሞላ ሊገዛ በቃ! ችግሩ በመጨረሻ የሚገዛው ግዛት ማለቁ ሲነገረው ስቅስቅ ብሎ ማልቀሱ ነው፡፡ ሰው ነዋ! አይረካም! ‹‹ሰው አለሙን ሁሉ ቢያተርፍ ነፍሱን ግን ቢያጎድል ምን ይጠቅመዋል›› እንዲል መጽሐፍ፡፡ ናፖሊዮን ቦናፖርት! ከአንድ ባታሊዮን ጦር አንድ ጋዜጠኛ የሚያስፈራው ንጉሥ ናፖሊዮን በወታደሮቹ መካከል በአጭር ቁመቱ እየተንጎራደደ የአንዱን ወታደር ስም ጠርቶ ‹‹ዤራርድ ቀና በል እንጂ!›› ይለዋል፡፡ አበቃ! ወታደሩ ሁሉ የኔንም ስም ያውቀዋል ብሎ ይደመድማል፡፡ የናፖሊዮን ጋዜጠኞችም ይህንኑ መሰል ወሬዎችን ሞቅ አድርገው ያራግባሉ፤በቃ በዚህ የተጠናና የተቀናበረ ያቀራረብ መልክም ናፖሊዮን በተጨናበረ አለማዊ ክብር ሽቅብ እየተመነደገ ፈረሱን ኮልኩሎ ይሸመጥጣል፤ሀገር ወዳዱ ምስኪን ዜጋ ለሀገር ሉአላዊነት ቢሆን ደግ፡ንጉሡ ጠብ ያለሽ በዳቦ እያለ አቧራ በሚያስነሳበት በየፍልሚያው ያለእዳው ነፍሱን ይገብራል። ለምን ቢል…ሀገር መክዳትን አይነት ከቀረው ዜጋ ጋር የሚያቃቅርና የሚያራርቅ በቀዬውና በየጎጡ የሚናፈስ ረቂቅ ወሬ ሴራ ይቀመርለታል! ካፍታ የማስታወቂያ ቆይታ በኋላ ይፈጠፈጣል! ከዚህ ይልቅስ የሂትለር ‹‹ወዳጅነትና እንክብካቤ›› ይምጣብኝ! ‹‹ያስጠራውህ ለስልጣኔ ስለምታሰጋኝ ልገድልህ ነው፤ ቢሆንም ግን ምንም ቢሆን ወዳጄ ነህና አንተ እንደማንኛውም ሰው አትሰናበትም፤እናም አይዞን! ቀብርህ በክብር የፊልድ ማርሻልነትህ ደረጃ በምናምን ሺህ ያህል መቶ ጄኔራሎች፣በምናምን ሺህ አለቃዎች ይከናወንልሀል። እንዴ ምን በወጣህ፤ወዳጄኮ ነህ! ህእ!›› ታዲያ  አሁንም ሚዲያ ነፍሴ የፊልድ ማርሻሉን እንቆቅልሽ የህልፈት ጉዳይ ትቶ ከአለም አንደኛ የሆነውን ጉደኛውን የቀብር ስርአቱን አግዝፎ ሲዘግብ ይገኛል። ምን ታመጣለህ አልክ….ልክ ነህ፡፡ አዎን ምንም አይባልም። ምንስ ሊባል ይችላልና…በአምባገነኖችና ክቡር እምክቡራኑ መዋእል ውስጥ አዲስ ነገር ነውን’ዴ ይኼ…ንጉስ ካሊጉላ ቢሰማ ግን ‹‹ሞት ራሱ ነው መሞት ያለበት›› ይልሀል፡፡

ማሪያን አንቶኔት፤ የትውልድ ሀገሯን ስዊዝን በስውር እየረዳች በሚዲያ ወከባዋ የፈረንሳይ አፍቃሪ ንግስት ነበረች፡፡ ጠኔ ሲያንገላታው የነበረው የሰፊው ህዝብ ሚዲያ በእንቁ እንደምትንቆጠቆጥ የደረሰባትና ያጋለጣት ጊዜ ግን የተገኘችው በእኩለ ሌሊት ወደ ሀገሯ ልትፈረጥጥ ስትሞክር ነበር፡፡ ድንበር ላይ፡፡ ጀንበር ስትፈነጥቅ አንገቷ እንደሚቀላ ስታውቀው በታሰረችበት ማቆያ ክፍል ውስጥ መአልቱን ጠጉሯ ጥጥ መስሎ ሸብቶ አደረ፡፡

ዘመናዊው የሚዲያ ጦስም ይህንኑ መንገድ ሲገፋበት እናያለን፡፡ ለከፍታም /ሽምጠጣ/ ለዝቅታም /ፍጥፈጣም። ከሽምጠጣ ብዙ ቀሽት ቀሽት የሆኑ የየዘመኑ የታሪክ ዝንጣፊ ድርሳናት አሉ፡፡ ግራ የሚያጋባው ፍጥፈጣ ከገጠማቸው መሀል ዝነኛ ዝነኛ የሆኑትን ለመጥቀስ ያህል ማይክል ጃክሰን ፆታው ‹ግራ› ነው፤ ቢል ክሊንተን ሞኒካን እነሆ በረከት አለ፤ ማራዶና ዕፀ ፋርስ አጤሰ፤ ከሀገራችን ደግሞ ቴዲ አፍሮ ጡት ላይ ፈረመ እና በእንትን ምክንያት ታረደን የጥላሁን ገሠሠን መጠቀስ ይቻላል፡፡ ‹‹የዜማው ንጉሥ!›› ጥላሁን አንድ ነገር ብቻ አለ…‹‹ሆድ ይፍጀው!›› … እሱኑ በዜማ ብናጅብለትስ… ‹‹አረ ተዉኝ፤ባትነኩኝ ምናለበት፤እባካችሁ ሰዎች ስራዬን ልስራበት…››

ፈጥፋጮቹ ባቀራረበባቸው የሚከተሉት ጥበብም ለተፈጥፋጩ /ለሚጠመድበት/ ከዚያው ከኦሪቱ አዳምና ሄዋን ከገጠማቸው ፈተና/ ወጥመድ ጋር ተመሳሳይ ነው። ‹‹መልኩ ያማረ ለመብላትም የሚያጓጓ›› እንደነበረ ስለ በለስ ፍሬ ተፅፏል፡፡ ሰው አፈር ነውና፤ፍፁም አይደለምና ይስታል፡፡ ያኔ ፈጥፋጭ ከች ይላል፡፡ ዘመናዊው አለም ደግሞ ይህንን ሁናቴ ‹‹የአኪሌዝ ተረከዝ›› ይለዋል። አኪሌዝ ምንም ጦርና ቀስት እንዳይወጋው እናቱ እግሩን ይዛ ምትሀተኛ ውኃ ውስጥ /ቡሌት ፕሩፍ ነገር አይነት/ ነከረችው፡፡ ምን ዋጋ አለው፤ ሰው ፍፁም አይደለም አይደል…በእጇ የያዘችው መዳፏ የሸፈነው የተረከዙ ክፍል በዚያ ‹‹ተአምረኛ›› ውሃ አልተነከረም ኖሮ ለውድቀቱ ሰበብ ሆነ፡፡

ዘመናዊው አለም መረጃን ለአይነተኛ አላማ ማስፈፀሚያነት ከማዋሉ ባሻገር እንደ ሸቀጥ መተዳደሪያ ማድረግን አጠናክሮ በገፋበት መጠን ደግሞ የሰብአዊነት ጉዳይ ጥያቄ ውስጥ መውደቁን የምናስተውለው ወጣቷን ልዕልት ዲያናን ቀን ተሌት በመከታተል አሳድደው አሳድደው ከፍፃሜዋ አፋፍ ላይ ካደረሷት በኋላም፤ በፎቶግራፍ ጥበብ ሩሕዋን፣ የነፍስ ህቅታዋን በምስል ለማስቀረት ሲጋፉ መታየታቸው ነው - ፓፓራዚዎች። የሙያ ፍቅርም ሊሆን ይችላል በእርግጥ፡፡ መረጃን ፈጥኖ ማቀበል የሚበረታታ ሙያ መሆኑን ባንክድም፤ወደ ድሀዋ ጎጇችን ትውፊታዊና ባህላዊ መስተጋብር ስንመጣ ግን፤መቸም ወፍ እንደ ሀገሩ ይጮሀልና ‹‹ካፍ ከወጣ አፋፍ››፣ ‹‹ጦር ከፈታው ወሬ የፈታው›› …ወዘተ በሚባልበትና መገናኛ ብዙኃን ያወሩት በፅኑ በሚታመንበት ማህበረሰብ መካከል የአንዳንድ አዕዋፍ የተኮረጁ ፉጨቶች /‹‹ፍጥፈጣዎች››/ የአንድ ወገን ዘገባዎች ጩኸት ‹‹ፍጥፈጣ›› በክቡሩ የሰው ልጅ ስብእና ላይ የሚያደርሱት የማይጠገን የመንፈስ ስብራት፤ በሰማዕታቱ የነፃነት ታጋዮች ክቡር ደም ህገ መንግስታዊ የዜግነት መብት በተጎናፀፈው ክቡር ዜጋ ላይ የሚፈጥሩት አሉታዊ አመለካከትና የሚያሳድሩት ማህበራዊ ተፅዕኖ በቀላሉ የሚታይ ጉዳይ አይደለም፡፡ ጽሙና ይስጠን! አሜን…

በዚህ አካሄድ ከቀጠልንና ምዕራባዊያንን የመኮረጅ ችሎታችን ረቀቅ እያለ ከመጣ’ኮ…ኦኦኦ! አደጋ ነው ወገን! የምር! አርቪንግ ዋላስ፤ መረጃ ያጣውን ተወዳጅ ጋዜጣ ላለመዝጋት ሲሉ ትኩስ/ያልተጣሩ/ለነጭ ባህልና አኗኗር የሚስማሙ የወንጀል ዜናዎችንና ራሱን ወንጀሉንም መስራት ስለጀመሩት የኤዲቶሪያል አባላት የፃፈውን መፅሀፉን ያስታውሷል፡፡ የሰው ልጅ ሆይ ወዴት እየሄድን ነው …በቅንነት ካየነውም ይህን መሰሉ በግለሰቦች ማንነትና ገመና ላይ ያነጣጠረ ክብረ ነክ የወሬ ማዕድ ለኢትዮጵያዊ ከሚሰጠው የሚዲያ /ሀሳብን የመግለፅ ነፃነት ትሩፋቱ ይልቅ መከባበርን የሚያጎድለው፣እውነትን የሚያራቁተው፣ እርስ በእርስ መተማመንን የሚሸረሽረው፣ በገዛ ሀገር ላይ የሚያሳቅቀው፣ ጥርጣሬን የሚያነግሰውና ሰላማዊ ኑሮን የሚያሽቆለቁለው …ወዘተ ነገሩ የበዛ ይመስለናል፡፡ የእውነት፡፡ ‹‹አይነፋም!›› እንዲል ያራዳ ልጅ ሰሞንኛ ቋንቋ፡፡ ሌሎች የሚያስጨንቁ የሚያንገበግቡ አጀንዳዎች የሉንም ማለት ነውስ…ከነገረ ቀደምስ፣ ዋናው ግብ ማለት መረጃው በህግ አግባብ ከመዳኘቱ በፊት ለሚሊዮኖች ለማድረስ የመጣደፉስ አካሂያድ ነገር የምር በቃ አላማው ምንድን ነው ያሰኛልም’ኮ አንዳንዴ። በተለይ በተለይ ደግሞ የሌላኛው ፅንፍ /የተፈጥፋጩ እንበለው…/ የመደመጥ መብት (the right to be heard) ገና ባልተስተናገደበት ሁኔታ ሚዛን ላይ ሲቀመጥ፡፡ ደርግ አንድን ዜጋ ከገደለ በኋላ ጉዳዩ ሲጣራና ዜጋው ንፁህ ሆኖ ሲገኝ ‹‹ለቤተሰቦቹ አብዮታዊ የይቅርታ ደብዳቤ ይፃፍላቸው!›› የምትል ብሂል ነበረችው አሉ፡፡ ቀልድ! (ጅብ ከሄደ ውሻ) የከበደ ሚካኤል ‹‹ጃፓን እንዴት ሰለጠነች››፣ የነጋድራስ ገብረህወት ባይከዳኝ ‹‹ህዝብና መንግስት አስተዳደር›› አይነት መጻህፍት፣ አስተሳሰቦችና አሳቢ አሰላሳዮች thinkers , visionaries ቢበረክቱላት ብለን የምንመኝላት፣ እትብታችን የተቀበረባት ሀገራችን ኢትዮጵያ የሁላችንም ምድር ናት፡፡ እናም ኢትዮጵያ ሀገራችንም መቼም ቢሆን ልጆቿን በእኩል አይን ነው የምታየው ብለን ነው በፅኑ የምናምነው እንግዲህ እስካሁን፡፡ ክብር ለሰብአዊነትና እኩልነት ቅድሚያ ለሚሰጡ ‹‹ነፃ›› ሚዲያዎች ይሁን!

እግዚአብሔር ከሚፀየፋቸው ነገሮች አንዱ በወንድማማቾች መካከል ፀብን የሚዘራ ምላስን ነው ይላል ቅዱሱ መጽሀፍ፡፡ ዮሴፍ እግዚአብሔር የሰጠውን ራዕይ/ህልም ለመኖር ሲተጋ በጲጥፋራ እልፍኝ የደረሰበትን የ‹‹አስገድዶ መድፈር›› ውንጀላ በጋሻው ደሳለኝ በስብከቱ ሲተነትነው፤ ‹‹አድርጎት ቢሆን ኖሮ ጨርቁ /በንግስቲቱ ተበጭቆ ኤግዚቢት የሆነበት/ ከፊቱ ነበር የሚቀደደው፤ ውሸት የሆነ ነገር ሁሉ ከኋላ ነው የሚጎለጎለው…ዮሴፍ ንግሥቲቱ እጮሃለው ስትለው እግዚአብሔር ዘለአለም ከሚጮህብኝ እሷ አንድ ጊዜ ትጩህ ብሎ ፈቀደና ራሱን ለእስር፣ ለእግር ብረት ዳረገ›› ብሏል፡፡……ማንም ፍፁም አይደለም ማለቱስ አይደለም ወይ ክርስቶስ ‹‹በራስህ አይን ያለውን ግንድ ሳታወጣ፤በሰው አይን ያለውን ጉድፍ ላውጣ አትበል›› ወይም ‹‹ከናንተ ኃጢአት የሌለበት የመጀመሪያውን ድንጋ ይወርውር›› ማለቱ…

በሁለተኛው የአለም ጦርነት ዋዜማ አንድ አውሮጳዊ ጋዜጠኛ በድንገት ተነስቶ ‹‹በምድራችን ለሚከሰቱት ችግሮች ሁሉ መንስኤዎቹ አይሁዳዊያን ናቸው!›› አለ። በቃ! አይሁዳዊያን ‹‹ተፈጠፈጡ››! … ከአሰቃቂው የኦሽዊትዝ ካምፕ የሰቆቃ ህይወት ምስኪን ወላጅ እናት፣ አባቱንና ሁለት እህቶቹን አጥቶ ብቻውን በተአምር የተረፈው ኤሊ ዊዝል ‹‹ናይት›› በሚል ርዕስ የመከራ ዘመን ታሪኩን ባሰፈረበት መፅሀፉ፣የኖቤል ሽልማት ተሸላሚ ሆኖ መድረክ ላይ ሲቆም ፤የሰው ልጆችን ወደ ጥፋት በሚነዱ ድርጊቶች የተሰማሩ ሰዎች በህሊናቸው እንዲያመዛዝኑና ሰፋ አድርገውም እንዲያስተውሉ አበክሮ ሲገልጽ፤ በአለም ላይ ሰላማዊ አየር እንዲሰፍን ባስተላለፈው ምኞቱ መካከል በተለየ ሁኔታ ስማቸውን ከጠራቸው ሀገራት አንዷ ኢትዮጵያ ናት፡፡ ኤሊ ዊዝል እንባ ባቀረሩ አይኖቹ ታዳሚውን ትክ ብሎ እያየ በእብራይስጥ ቋንቋ ‹‹ከዚያ ሁሉ መአት ያተረፈኝ የእስራኤል አምላክ ይባረክ ›› አለና ጥቂት ፋታ አድርጎ የመጨረሻውን ዓረፍተ ነገር ተናግሮ ከመድረክ ወረደ። ‹‹እነሆ፤ ሁሉም ያልፋል፡፡ ያም ሆኖ ግን በክፉ ሰዎች የተነሳ የደረሰብኝን መራራ ግፍ መቼም መቼም መቼም ቢሆን በፍፁም አልረሳውም!!!››

ፈጣሪ ሀገራችን ኢትዮጵያን ይባርክልን፡፡ አሜን፡፡

 

   ‹‹አብዮት፤ አበየ ፤እምቢ አለ ከሚለው የግዕዝ ቃል የመጣ ነው›› የሚለው ዬኔታ ስብሀት፤ የመጀመሪያው አብዮተኛ ሰይጣን ዲያቢሎስ ነው ይላል፡፡ በእንግዳና ተቆርቋሪም ‹‹ጋዜጠኛ›› መሳይ አቀራረብ ‹‹በእውኑ እግዚአብሔር ከዚህ በገነት መካከል ከሚገኘው ፍሬ እንዳትበሉ አዝዟልን…›› በሚል ህልውናን ተፈታታኝ ጥያቄ አብዮቱን ያቀጣጠለባቸው ምስኪኖቹ አዳምና ሄዋን ግን ‹‹ሰው›› ነበሩ፡፡ የሰው ልጅ ታሪክ የሚጀምረው ከውድቀት ነው፡፡ ‹‹ሰው አፈር ነው አሉ፤ ሰው አፈር ነወይ…አዬ ሰው አፈር ነወይ…›› ትላለች ሙሾ አውራጅ፡፡ አዎ እናቴ! ያውም ስድስት ክንድ መሬት ውስጥ ኩርምት ብሎ የሚረሳ ነዋ! አስከሬኑም ከሌሎች እንስሳት አንጻር ለመበላሸት ይቸኩላል፡፡ ‹‹የኔ ቢጤው›› ደግሞ ያውም ከስህተቱ የማይማር፤ታጥቦ ጭቃ! እንዴት ማለት መልካም…በዚያው በኦሪት አቀራረብ በሰዎች መካከል ጠብንና አለመተማመንን መዝራት ተለምዶ! ምነው…አይባልም! ነውር ነው! ፋሽን ሁኗላ! እናም በአለም ላይ የመጀመሪያው ቀጣፊና ዋሾ ሰውን አሳተ! ቃየን ተወለደ። ‹‹ያዳቆነ ሰይጣን ሳያቀስስ አይመለስም›› የኦሪት ተረት ነች መሰለኝ፡፡ ሴጣን ዲያቢሎስ ዳግም በቃየን ልብ ቅናት ሆኖ ገብቶ አቤልን አስገደለ!

 ይህን መንገድ ገና በዘፍጥረት በኖሩ ሰዎች ላይ ስናየው ባይገርመንም አሁን ላይ ቆመን አወራረዱ ሰውን ምንኛ ከራሱ ጋር እንዳቆራረጠው ስናስተውል ግን ዘግናኝ ሆኖ ይገኛል፡፡ ማን ነበር ‹‹አላዋቂን ብታስደምም ተመራማሪን ታስቀይማለህ›› ያለው…እህ! ይኸዋ ያንኑ የቀድሞውን የኦሪት አልባስ ‹‹ሰው›› በልኩ እያስጠበበና እያስሰፋ ሲለብሰው ይኖራል፡፡ ታላቁ እስክንድር የአምላከ አማልእክቱ የዜዩስ ልጅ ነኝ፡ ፈረሴም እንዲሁ! አለ። ሸመጠጠ፡፡ በአፍ የተናፈሰ ገድሉ ገና በሩቁ የሰሙትን ሁሉ እያርበደበደ አለምን በሞላ ሊገዛ በቃ! ችግሩ በመጨረሻ የሚገዛው ግዛት ማለቁ ሲነገረው ስቅስቅ ብሎ ማልቀሱ ነው፡፡ ሰው ነዋ! አይረካም! ‹‹ሰው አለሙን ሁሉ ቢያተርፍ ነፍሱን ግን ቢያጎድል ምን ይጠቅመዋል›› እንዲል መጽሐፍ፡፡ ናፖሊዮን ቦናፖርት! ከአንድ ባታሊዮን ጦር አንድ ጋዜጠኛ የሚያስፈራው ንጉሥ ናፖሊዮን በወታደሮቹ መካከል በአጭር ቁመቱ እየተንጎራደደ የአንዱን ወታደር ስም ጠርቶ ‹‹ዤራርድ ቀና በል እንጂ!›› ይለዋል፡፡ አበቃ! ወታደሩ ሁሉ የኔንም ስም ያውቀዋል ብሎ ይደመድማል፡፡ የናፖሊዮን ጋዜጠኞችም ይህንኑ መሰል ወሬዎችን ሞቅ አድርገው ያራግባሉ፤በቃ በዚህ የተጠናና የተቀናበረ ያቀራረብ መልክም ናፖሊዮን በተጨናበረ አለማዊ ክብር ሽቅብ እየተመነደገ ፈረሱን ኮልኩሎ ይሸመጥጣል፤ሀገር ወዳዱ ምስኪን ዜጋ ለሀገር ሉአላዊነት ቢሆን ደግ፡ንጉሡ ጠብ ያለሽ በዳቦ እያለ አቧራ በሚያስነሳበት በየፍልሚያው ያለእዳው ነፍሱን ይገብራል። ለምን ቢል…ሀገር መክዳትን አይነት ከቀረው ዜጋ ጋር የሚያቃቅርና የሚያራርቅ በቀዬውና በየጎጡ የሚናፈስ ረቂቅ ወሬ ሴራ ይቀመርለታል! ካፍታ የማስታወቂያ ቆይታ በኋላ ይፈጠፈጣል! ከዚህ ይልቅስ የሂትለር ‹‹ወዳጅነትና እንክብካቤ›› ይምጣብኝ! ‹‹ያስጠራውህ ለስልጣኔ ስለምታሰጋኝ ልገድልህ ነው፤ ቢሆንም ግን ምንም ቢሆን ወዳጄ ነህና አንተ እንደማንኛውም ሰው አትሰናበትም፤እናም አይዞን! ቀብርህ በክብር የፊልድ ማርሻልነትህ ደረጃ በምናምን ሺህ ያህል መቶ ጄኔራሎች፣በምናምን ሺህ አለቃዎች ይከናወንልሀል። እንዴ ምን በወጣህ፤ወዳጄኮ ነህ! ህእ!›› ታዲያ  አሁንም ሚዲያ ነፍሴ የፊልድ ማርሻሉን እንቆቅልሽ የህልፈት ጉዳይ ትቶ ከአለም አንደኛ የሆነውን ጉደኛውን የቀብር ስርአቱን አግዝፎ ሲዘግብ ይገኛል። ምን ታመጣለህ አልክ….ልክ ነህ፡፡ አዎን ምንም አይባልም። ምንስ ሊባል ይችላልና…በአምባገነኖችና ክቡር እምክቡራኑ መዋእል ውስጥ አዲስ ነገር ነውን’ዴ ይኼ…ንጉስ ካሊጉላ ቢሰማ ግን ‹‹ሞት ራሱ ነው መሞት ያለበት›› ይልሀል፡፡

ማሪያን አንቶኔት፤ የትውልድ ሀገሯን ስዊዝን በስውር እየረዳች በሚዲያ ወከባዋ የፈረንሳይ አፍቃሪ ንግስት ነበረች፡፡ ጠኔ ሲያንገላታው የነበረው የሰፊው ህዝብ ሚዲያ በእንቁ እንደምትንቆጠቆጥ የደረሰባትና ያጋለጣት ጊዜ ግን የተገኘችው በእኩለ ሌሊት ወደ ሀገሯ ልትፈረጥጥ ስትሞክር ነበር፡፡ ድንበር ላይ፡፡ ጀንበር ስትፈነጥቅ አንገቷ እንደሚቀላ ስታውቀው በታሰረችበት ማቆያ ክፍል ውስጥ መአልቱን ጠጉሯ ጥጥ መስሎ ሸብቶ አደረ፡፡

ዘመናዊው የሚዲያ ጦስም ይህንኑ መንገድ ሲገፋበት እናያለን፡፡ ለከፍታም /ሽምጠጣ/ ለዝቅታም /ፍጥፈጣም። ከሽምጠጣ ብዙ ቀሽት ቀሽት የሆኑ የየዘመኑ የታሪክ ዝንጣፊ ድርሳናት አሉ፡፡ ግራ የሚያጋባው ፍጥፈጣ ከገጠማቸው መሀል ዝነኛ ዝነኛ የሆኑትን ለመጥቀስ ያህል ማይክል ጃክሰን ፆታው ‹ግራ› ነው፤ ቢል ክሊንተን ሞኒካን እነሆ በረከት አለ፤ ማራዶና ዕፀ ፋርስ አጤሰ፤ ከሀገራችን ደግሞ ቴዲ አፍሮ ጡት ላይ ፈረመ እና በእንትን ምክንያት ታረደን የጥላሁን ገሠሠን መጠቀስ ይቻላል፡፡ ‹‹የዜማው ንጉሥ!›› ጥላሁን አንድ ነገር ብቻ አለ…‹‹ሆድ ይፍጀው!›› … እሱኑ በዜማ ብናጅብለትስ… ‹‹አረ ተዉኝ፤ባትነኩኝ ምናለበት፤እባካችሁ ሰዎች ስራዬን ልስራበት…››

ፈጥፋጮቹ ባቀራረበባቸው የሚከተሉት ጥበብም ለተፈጥፋጩ /ለሚጠመድበት/ ከዚያው ከኦሪቱ አዳምና ሄዋን ከገጠማቸው ፈተና/ ወጥመድ ጋር ተመሳሳይ ነው። ‹‹መልኩ ያማረ ለመብላትም የሚያጓጓ›› እንደነበረ ስለ በለስ ፍሬ ተፅፏል፡፡ ሰው አፈር ነውና፤ፍፁም አይደለምና ይስታል፡፡ ያኔ ፈጥፋጭ ከች ይላል፡፡ ዘመናዊው አለም ደግሞ ይህንን ሁናቴ ‹‹የአኪሌዝ ተረከዝ›› ይለዋል። አኪሌዝ ምንም ጦርና ቀስት እንዳይወጋው እናቱ እግሩን ይዛ ምትሀተኛ ውኃ ውስጥ /ቡሌት ፕሩፍ ነገር አይነት/ ነከረችው፡፡ ምን ዋጋ አለው፤ ሰው ፍፁም አይደለም አይደል…በእጇ የያዘችው መዳፏ የሸፈነው የተረከዙ ክፍል በዚያ ‹‹ተአምረኛ›› ውሃ አልተነከረም ኖሮ ለውድቀቱ ሰበብ ሆነ፡፡

ዘመናዊው አለም መረጃን ለአይነተኛ አላማ ማስፈፀሚያነት ከማዋሉ ባሻገር እንደ ሸቀጥ መተዳደሪያ ማድረግን አጠናክሮ በገፋበት መጠን ደግሞ የሰብአዊነት ጉዳይ ጥያቄ ውስጥ መውደቁን የምናስተውለው ወጣቷን ልዕልት ዲያናን ቀን ተሌት በመከታተል አሳድደው አሳድደው ከፍፃሜዋ አፋፍ ላይ ካደረሷት በኋላም፤ በፎቶግራፍ ጥበብ ሩሕዋን፣ የነፍስ ህቅታዋን በምስል ለማስቀረት ሲጋፉ መታየታቸው ነው - ፓፓራዚዎች። የሙያ ፍቅርም ሊሆን ይችላል በእርግጥ፡፡ መረጃን ፈጥኖ ማቀበል የሚበረታታ ሙያ መሆኑን ባንክድም፤ወደ ድሀዋ ጎጇችን ትውፊታዊና ባህላዊ መስተጋብር ስንመጣ ግን፤መቸም ወፍ እንደ ሀገሩ ይጮሀልና ‹‹ካፍ ከወጣ አፋፍ››፣ ‹‹ጦር ከፈታው ወሬ የፈታው›› …ወዘተ በሚባልበትና መገናኛ ብዙኃን ያወሩት በፅኑ በሚታመንበት ማህበረሰብ መካከል የአንዳንድ አዕዋፍ የተኮረጁ ፉጨቶች /‹‹ፍጥፈጣዎች››/ የአንድ ወገን ዘገባዎች ጩኸት ‹‹ፍጥፈጣ›› በክቡሩ የሰው ልጅ ስብእና ላይ የሚያደርሱት የማይጠገን የመንፈስ ስብራት፤ በሰማዕታቱ የነፃነት ታጋዮች ክቡር ደም ህገ መንግስታዊ የዜግነት መብት በተጎናፀፈው ክቡር ዜጋ ላይ የሚፈጥሩት አሉታዊ አመለካከትና የሚያሳድሩት ማህበራዊ ተፅዕኖ በቀላሉ የሚታይ ጉዳይ አይደለም፡፡ ጽሙና ይስጠን! አሜን…

በዚህ አካሄድ ከቀጠልንና ምዕራባዊያንን የመኮረጅ ችሎታችን ረቀቅ እያለ ከመጣ’ኮ…ኦኦኦ! አደጋ ነው ወገን! የምር! አርቪንግ ዋላስ፤ መረጃ ያጣውን ተወዳጅ ጋዜጣ ላለመዝጋት ሲሉ ትኩስ/ያልተጣሩ/ለነጭ ባህልና አኗኗር የሚስማሙ የወንጀል ዜናዎችንና ራሱን ወንጀሉንም መስራት ስለጀመሩት የኤዲቶሪያል አባላት የፃፈውን መፅሀፉን ያስታውሷል፡፡ የሰው ልጅ ሆይ ወዴት እየሄድን ነው …በቅንነት ካየነውም ይህን መሰሉ በግለሰቦች ማንነትና ገመና ላይ ያነጣጠረ ክብረ ነክ የወሬ ማዕድ ለኢትዮጵያዊ ከሚሰጠው የሚዲያ /ሀሳብን የመግለፅ ነፃነት ትሩፋቱ ይልቅ መከባበርን የሚያጎድለው፣እውነትን የሚያራቁተው፣ እርስ በእርስ መተማመንን የሚሸረሽረው፣ በገዛ ሀገር ላይ የሚያሳቅቀው፣ ጥርጣሬን የሚያነግሰውና ሰላማዊ ኑሮን የሚያሽቆለቁለው …ወዘተ ነገሩ የበዛ ይመስለናል፡፡ የእውነት፡፡ ‹‹አይነፋም!›› እንዲል ያራዳ ልጅ ሰሞንኛ ቋንቋ፡፡ ሌሎች የሚያስጨንቁ የሚያንገበግቡ አጀንዳዎች የሉንም ማለት ነውስ…ከነገረ ቀደምስ፣ ዋናው ግብ ማለት መረጃው በህግ አግባብ ከመዳኘቱ በፊት ለሚሊዮኖች ለማድረስ የመጣደፉስ አካሂያድ ነገር የምር በቃ አላማው ምንድን ነው ያሰኛልም’ኮ አንዳንዴ። በተለይ በተለይ ደግሞ የሌላኛው ፅንፍ /የተፈጥፋጩ እንበለው…/ የመደመጥ መብት (the right to be heard) ገና ባልተስተናገደበት ሁኔታ ሚዛን ላይ ሲቀመጥ፡፡ ደርግ አንድን ዜጋ ከገደለ በኋላ ጉዳዩ ሲጣራና ዜጋው ንፁህ ሆኖ ሲገኝ ‹‹ለቤተሰቦቹ አብዮታዊ የይቅርታ ደብዳቤ ይፃፍላቸው!›› የምትል ብሂል ነበረችው አሉ፡፡ ቀልድ! (ጅብ ከሄደ ውሻ) የከበደ ሚካኤል ‹‹ጃፓን እንዴት ሰለጠነች››፣ የነጋድራስ ገብረህወት ባይከዳኝ ‹‹ህዝብና መንግስት አስተዳደር›› አይነት መጻህፍት፣ አስተሳሰቦችና አሳቢ አሰላሳዮች thinkers , visionaries ቢበረክቱላት ብለን የምንመኝላት፣ እትብታችን የተቀበረባት ሀገራችን ኢትዮጵያ የሁላችንም ምድር ናት፡፡ እናም ኢትዮጵያ ሀገራችንም መቼም ቢሆን ልጆቿን በእኩል አይን ነው የምታየው ብለን ነው በፅኑ የምናምነው እንግዲህ እስካሁን፡፡ ክብር ለሰብአዊነትና እኩልነት ቅድሚያ ለሚሰጡ ‹‹ነፃ›› ሚዲያዎች ይሁን!

እግዚአብሔር ከሚፀየፋቸው ነገሮች አንዱ በወንድማማቾች መካከል ፀብን የሚዘራ ምላስን ነው ይላል ቅዱሱ መጽሀፍ፡፡ ዮሴፍ እግዚአብሔር የሰጠውን ራዕይ/ህልም ለመኖር ሲተጋ በጲጥፋራ እልፍኝ የደረሰበትን የ‹‹አስገድዶ መድፈር›› ውንጀላ በጋሻው ደሳለኝ በስብከቱ ሲተነትነው፤ ‹‹አድርጎት ቢሆን ኖሮ ጨርቁ /በንግስቲቱ ተበጭቆ ኤግዚቢት የሆነበት/ ከፊቱ ነበር የሚቀደደው፤ ውሸት የሆነ ነገር ሁሉ ከኋላ ነው የሚጎለጎለው…ዮሴፍ ንግሥቲቱ እጮሃለው ስትለው እግዚአብሔር ዘለአለም ከሚጮህብኝ እሷ አንድ ጊዜ ትጩህ ብሎ ፈቀደና ራሱን ለእስር፣ ለእግር ብረት ዳረገ›› ብሏል፡፡……ማንም ፍፁም አይደለም ማለቱስ አይደለም ወይ ክርስቶስ ‹‹በራስህ አይን ያለውን ግንድ ሳታወጣ፤በሰው አይን ያለውን ጉድፍ ላውጣ አትበል›› ወይም ‹‹ከናንተ ኃጢአት የሌለበት የመጀመሪያውን ድንጋ ይወርውር›› ማለቱ…

በሁለተኛው የአለም ጦርነት ዋዜማ አንድ አውሮጳዊ ጋዜጠኛ በድንገት ተነስቶ ‹‹በምድራችን ለሚከሰቱት ችግሮች ሁሉ መንስኤዎቹ አይሁዳዊያን ናቸው!›› አለ። በቃ! አይሁዳዊያን ‹‹ተፈጠፈጡ››! … ከአሰቃቂው የኦሽዊትዝ ካምፕ የሰቆቃ ህይወት ምስኪን ወላጅ እናት፣ አባቱንና ሁለት እህቶቹን አጥቶ ብቻውን በተአምር የተረፈው ኤሊ ዊዝል ‹‹ናይት›› በሚል ርዕስ የመከራ ዘመን ታሪኩን ባሰፈረበት መፅሀፉ፣የኖቤል ሽልማት ተሸላሚ ሆኖ መድረክ ላይ ሲቆም ፤የሰው ልጆችን ወደ ጥፋት በሚነዱ ድርጊቶች የተሰማሩ ሰዎች በህሊናቸው እንዲያመዛዝኑና ሰፋ አድርገውም እንዲያስተውሉ አበክሮ ሲገልጽ፤ በአለም ላይ ሰላማዊ አየር እንዲሰፍን ባስተላለፈው ምኞቱ መካከል በተለየ ሁኔታ ስማቸውን ከጠራቸው ሀገራት አንዷ ኢትዮጵያ ናት፡፡ ኤሊ ዊዝል እንባ ባቀረሩ አይኖቹ ታዳሚውን ትክ ብሎ እያየ በእብራይስጥ ቋንቋ ‹‹ከዚያ ሁሉ መአት ያተረፈኝ የእስራኤል አምላክ ይባረክ ›› አለና ጥቂት ፋታ አድርጎ የመጨረሻውን ዓረፍተ ነገር ተናግሮ ከመድረክ ወረደ። ‹‹እነሆ፤ ሁሉም ያልፋል፡፡ ያም ሆኖ ግን በክፉ ሰዎች የተነሳ የደረሰብኝን መራራ ግፍ መቼም መቼም መቼም ቢሆን በፍፁም አልረሳውም!!!››

ፈጣሪ ሀገራችን ኢትዮጵያን ይባርክልን፡፡ አሜን፡፡

 

 

 

 

Read 1908 times