Print this page
Tuesday, 26 May 2015 08:05

የምዕራብ አፍሪካ መሪዎች የስልጣን ዘመናቸው እንዳይገደብ ወሰኑ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 

 

 

   የምዕራብ አፍሪካ አገራት ፕሬዚዳንቶች ከሁለት ዙር በላይ በስልጣን ላይ እንዳይቆዩ ለማድረግ ታልሞ የቀረበውን የስልጣን ገደብ የሚያስቀምጥ ክልላዊ የስምምነት ሃሳብ፣ የአገራቱ መሪዎች ውድቅ እንዳደረጉት ቢቢሲ ዘገበ፡፡

የአገራቱ መሪዎች ባለፈው ማክሰኞ በጋና መዲና አክራ ባካሄዱት የኮሜሳ ክልላዊ ስብሰባ ላይ፣ በሃሳቡ ዙሪያ መምከራቸውንና ለጊዜው ሃሳቡን ውድቅ ማድረጋቸውን የጠቆመው ዘገባው፣ ከሁለት ዙር በላይ በስልጣን ላይ በቆዩ መሪዎች በመመራት ላይ ያሉት ቶጎ እና ጋምቢያ የስልጣን ዘመን ገደቡን አጥብቀው እንደተቃወሙት ገልጿል፡፡ አብዛኞቹ የምእራብ አፍሪካ አገራት በህገ-መንግስቶቻቸው አንድ ፕሬዚዳንት ከሁለት ዙር በላይ በስልጣን ላይ መቆየት እንደማይችል ቢደነግጉም፣ በተቃራኒው ከዚህ ገደብ አልፈው በስልጣናቸው የሚቆዩ መሪዎች አሉ ብሏል ዘገባው፡፡

አንዳንድ የምእራብ አፍሪካ አገራት መሪዎች በጉዳዩ ዙሪያ በሰጡት አስተያየት፣ እያንዳንዱ አገር የየራሱ የሆነ የተለያየ የፖለቲካ አውድ ውስጥ የሚገኝ እንደመሆኑ፣ በሁሉም አገራት ላይ ተፈጻሚ የሚሆን አንድ አይነት ህግ መተግበር አግባብ አይደለም ብለዋል፡፡  

አስተያየት ሰጪዎች በበኩላቸው፤ የፕሬዚዳንቶችን የስልጣን ዘመን ቆይታ በክልላዊ ደረጃ በህግ መገደብ የሚለው ሃሳብ በስብሰባው ላይ ራሱን የቻለ የመወያያ አጀንዳ ሆኖ መቅረቡ እንደ አንድ የለውጥ ምእራፍ የሚታይ ነው ብለዋል፡፡ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የምእራብ አፍሪካ ተወካይ የሆኑት ሞሃመድ ኢብን ቻምፓስ  እቅዱን እንደሚደግፉት ገልጸው፣ ሃሳቡ የተጠነሰሰው የቡርኪናፋሶው ፕሬዚዳንት ብሌስ ኮምፓዎሬ ባለፈው አመት የአገሪቱን ህገመንግስት አንቀጽ በማሻሻል ለሶስተኛ ዙር በስልጣን ላይ ለመቆየት ያልተሳካ ሙከራ ማድረጋቸውን ተከትሎ እንደሆነ አስታውሰዋል፡፡

በአገራቱ መሪዎች ላይ የስልጣን ገደብ ለማስቀመጥ ታስቦ የተዘጋጀው ይህ እቅድ፤ ተጨማሪ ውይይት እንዲደረግበት መሪዎቹ ስምምነት ላይ መድረሳቸውን ያስታወቀው ዘገባው፣ የቶጎው ፕሬዚዳንት ፋኦሪ ጋሲንግቤ ለሶስተኛ፣ የጋምቢያው ፕሬዚዳንት  ያህያ ጃሜህ ደግሞ ለአራተኛ ዙር የስልጣን ዘመን አገራቱን እየመሩ እንደሚገኙም ጠቁሟል፡፡

   የምዕራብ አፍሪካ አገራት ፕሬዚዳንቶች ከሁለት ዙር በላይ በስልጣን ላይ እንዳይቆዩ ለማድረግ ታልሞ የቀረበውን የስልጣን ገደብ የሚያስቀምጥ ክልላዊ የስምምነት ሃሳብ፣ የአገራቱ መሪዎች ውድቅ እንዳደረጉት ቢቢሲ ዘገበ፡፡

የአገራቱ መሪዎች ባለፈው ማክሰኞ በጋና መዲና አክራ ባካሄዱት የኮሜሳ ክልላዊ ስብሰባ ላይ፣ በሃሳቡ ዙሪያ መምከራቸውንና ለጊዜው ሃሳቡን ውድቅ ማድረጋቸውን የጠቆመው ዘገባው፣ ከሁለት ዙር በላይ በስልጣን ላይ በቆዩ መሪዎች በመመራት ላይ ያሉት ቶጎ እና ጋምቢያ የስልጣን ዘመን ገደቡን አጥብቀው እንደተቃወሙት ገልጿል፡፡ አብዛኞቹ የምእራብ አፍሪካ አገራት በህገ-መንግስቶቻቸው አንድ ፕሬዚዳንት ከሁለት ዙር በላይ በስልጣን ላይ መቆየት እንደማይችል ቢደነግጉም፣ በተቃራኒው ከዚህ ገደብ አልፈው በስልጣናቸው የሚቆዩ መሪዎች አሉ ብሏል ዘገባው፡፡

አንዳንድ የምእራብ አፍሪካ አገራት መሪዎች በጉዳዩ ዙሪያ በሰጡት አስተያየት፣ እያንዳንዱ አገር የየራሱ የሆነ የተለያየ የፖለቲካ አውድ ውስጥ የሚገኝ እንደመሆኑ፣ በሁሉም አገራት ላይ ተፈጻሚ የሚሆን አንድ አይነት ህግ መተግበር አግባብ አይደለም ብለዋል፡፡  

አስተያየት ሰጪዎች በበኩላቸው፤ የፕሬዚዳንቶችን የስልጣን ዘመን ቆይታ በክልላዊ ደረጃ በህግ መገደብ የሚለው ሃሳብ በስብሰባው ላይ ራሱን የቻለ የመወያያ አጀንዳ ሆኖ መቅረቡ እንደ አንድ የለውጥ ምእራፍ የሚታይ ነው ብለዋል፡፡ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የምእራብ አፍሪካ ተወካይ የሆኑት ሞሃመድ ኢብን ቻምፓስ  እቅዱን እንደሚደግፉት ገልጸው፣ ሃሳቡ የተጠነሰሰው የቡርኪናፋሶው ፕሬዚዳንት ብሌስ ኮምፓዎሬ ባለፈው አመት የአገሪቱን ህገመንግስት አንቀጽ በማሻሻል ለሶስተኛ ዙር በስልጣን ላይ ለመቆየት ያልተሳካ ሙከራ ማድረጋቸውን ተከትሎ እንደሆነ አስታውሰዋል፡፡

በአገራቱ መሪዎች ላይ የስልጣን ገደብ ለማስቀመጥ ታስቦ የተዘጋጀው ይህ እቅድ፤ ተጨማሪ ውይይት እንዲደረግበት መሪዎቹ ስምምነት ላይ መድረሳቸውን ያስታወቀው ዘገባው፣ የቶጎው ፕሬዚዳንት ፋኦሪ ጋሲንግቤ ለሶስተኛ፣ የጋምቢያው ፕሬዚዳንት  ያህያ ጃሜህ ደግሞ ለአራተኛ ዙር የስልጣን ዘመን አገራቱን እየመሩ እንደሚገኙም ጠቁሟል፡፡

 

 

 

Read 1301 times
Administrator

Latest from Administrator