Monday, 25 May 2015 07:51

በምርጫ ጣቢያዎች ጥብቅ ፍተሻና ጥበቃ ይደረጋል ተባለ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ምርጫ ቦርድ በህገወጦች ላይ የከፋ እርምጃ እወስዳለሁ ብሏል
ሞባይል ስልክ ይዞ መግባት አይፈቀድም

ነገ በሚካሄደው 5ኛው አገር አቀፍ ምርጫ ላይ በየምርጫ ጣቢያዎቹ ጥብቅ ፍተሻና ጥበቃ እንደሚደረግ የጠቆመው ምርጫ ቦርድ፤ ከህግና ሥርዓት ውጪ ሆነው በተገኙ ወገኖች ላይ ጥብቅ እርምጃ እንደሚወሰድ አስታወቀ፡፡ መራጮች ወደ ምርጫ ጣቢያዎች በሚሄዱበት ወቅት ከምርጫ ካርዳቸውና ከመታወቂያ ወረቀታቸው ሌላ ምንም አይነት ነገሮችን ይዘው መግባት እንደማይፈቀድላቸውም ተገልጿል፡፡
የምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ፕሮፌሰር መርጋ በቃና ከትናንት በስቲያ በሒልተን ሆቴል በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንደተናገሩት፤ ምርጫው ሠላማዊ በሆነ መንገድ እንዲካሄድ ለማድረግ የሚያስችል ቅድመ - ዝግጅት ተጠናቋል፡፡ መራጮች ወደ ምርጫ ጣቢያ ሲሄዱ ሞባይል ስልካቸውንም ሆነ ሌላ ምንም ዓይነት መሣሪያዎችን ይዘው መግባት አይፈቀድላቸውም፡፡
የምርጫው በሰላማዊ መንገድ መጠናቀቅ የቦርዱ ኃላፊነት መሆኑን ያስገነዘቡት ፕሮፌሰር መርጋ፤ ይህንን ሁኔታ ለማስጠበቅም ሠላማዊ የምርጫ ሂደትን ለማደፍረስ በሚንቀሳቀሱ ወገኖች ላይ ቦርዱ የሚወስደው እርምጃ የከፋ ይሆናል ብለዋል፡፡ ለዚህ ደግሞ በቂ ዝግጅት ተደርጓል ሲሉ አስጠንቅቀዋል፡፡

Read 1448 times