Saturday, 16 May 2015 10:13

ባለ 43 ፎቁ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ

Written by 
Rate this item
(8 votes)

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በርዝመቱ ከምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ የሆነውን ህንፃ በአዲስ አበባ ለማስገንባት ከቻይናው የኮንስትራክሽን ኩባንያ ጋር ስምምነት መፈራረሙን ባንኩ አስታወቀ፡፡
ሕንፃው በጋንዲ መታሰቢያ ሆስፒታልና በኢትዮጵያ ሆቴል መካከል ባለው ስፍራ የሚሰራ ሲሆን 198 ሜትር ርዝመትና 43 ወለሎች እንዲሁም 1,500 መኪኖች ማቆም የሚችል 4 ቤዝመንት ወለል እንደሚኖሩት የባንኩ የኮሙኒኬሽን ሥራ አስኪያጅ አቶ ኤፍሬም መኩሪያ ገልፀዋል፡፡
ከዋናው ሕንፃ ጎን ሁለት ባለ 5 ፎቅ ሕንፃዎች እንደሚገነቡ የጠቀሱት አቶ ኤፍሬም፤ አንዱ የኮሜርሻል ሴንተር፣ ሁለተኛው የስብሰባ ማዕከል ነው ብለዋል፡፡ ትልቁ የስብሰባ አዳራሽ 2000 ሰዎች የመያዝ አቅም ሲኖረው፣ ሌሎቹ አዳራሾች 300 ሰዎች 5 አዳራሾች ደግሞ 200 ሰዎች እንደሚይዙና የዘመኑ የቴክኖሎጂ ውጤት የሆኑ መሳሪያዎች እንደሚገጠሙላቸው ጠቁመው ግንባታው ከሜይ 2015 ጀምሮ በ4 ዓመት ውስጥ እንደሚጠናቀቅ አቶ ኤፍሬም ተናግረዋል፡፡

Read 6950 times