Saturday, 16 May 2015 10:11

ብሌስ አግሮ ፉድ ላቦራቶሪ ደረጃ እንዲሰጥ ተፈቀደለት

Written by  መንግሥቱ አበበ
Rate this item
(0 votes)

የኢትዮጵያ ደረጃዎች ኤጀንሲ በምግብ፣ በመጠጥና በእንስሳት መኖ በኢትዮጵያ አስገዳጅ ደረጃ በወጣላቸው ምርቶች ብቻ የደረጃዎች ምልክት እንዲሰጥ ለብሌስ አግሪ ፉድ ላቦራቶሪ ፈቃድ ሰጠ፡፡
ኤጀንሲው ለብሌስ አግሪ ፉድ ላቦራቶሪ በጻፈው ደብዳቤ፤ ከግንቦት 3 ቀን 2007 ጀምሮ በምግብ፣ በመጠጥና የእንስሳት መኖ በመሳሰሉ ምርቶች ላይ ኤጀንሲው ባዘጋጀው የሰርቲፊኬሽን መመሪያ መሰረት፤ በኢትዮጵያ ደረጃ በወጣላቸው ምርቶች ብቻ የደረጃዎች ምልክት እንዲሰጥ ፈቅዷል፡፡
ብሌስ አግሪ ፉድ ላቦራቶሪ በምግብ፣ በመጠጥና በእንስሳት መኖ በመሳሰሉ ምርቶች ላይ የላቦራቶሪ ፍተሻ፣ ኢንስፔክሽንና ሰርቲፊኬሽን አገልግሎት የሚሰጥ ሲሆን ላቦራቶሪው ዓለም አቀፍ እውቅና ያለውና ለአምራቾች፣ ለላኪዎችና ለአገልግሎት ሰጪዎች ተዓማኒነት ያለው አገልግሎት እንደሚሰጥ ታውቋል፡፡
ብሌስ ላቦራቶሪ በትምህርት ሚ/ር ቅድመ እውቅና ያለው ሲሆን በራሱ የሥልጠና ኢንስቲትዩት በሥነ - ምግብ፣ በምግብ ደህንነት፣ በተለያዩ ምግቦች አዘገጃጀትና የላቦራቶሪ አናሊስስ ስልጠና ይሰጣል፡፡   

Read 1550 times