Saturday, 02 May 2015 12:00

የጃፓኑ ባቡር የአለማችንን የፍጥነት ክብረ ወሰን ሰበረ

Written by 
Rate this item
(2 votes)

 በሰከንድ 10 ማይል፤ በሰዓት 603 ኪ.ሜ ይፈተለካል

በአለማችን በፍጥነቱ አቻ የማይገኝለት የተባለውና በጃፓን የተሰራው ፈጣን ባቡር ባለፈው ማክሰኞ ከብረወሰን ባስመዘገበ ፍጥነት የሙከራ ጉዞ ማድረጉን ሲኤንኤን ዘገበ፡፡በጃፓኗ ያማናሺ ከተማ የሙከራ ጉዞ ያደረገው ባቡሩ፤ በሰዓት 603 ኪሊ ሜትር ፍጥነት ሲጓዝ ያዩት የአካባቢዋ ነዋሪዎች ያዩትን ነገር ለማመን ተቸግረው እንደነበር ዘገባው ገልጧል፡፡
እ.ኤ.አ በ2027 መደበኛ አገልግሎት መስጠት ይጀምራል ተብሎ የሚጠበቀው ይሄው ፈጣን ባቡር፣ ከተለመደው አካሄድ በተለየ ሃዲዱን ሳይነካ በማግኔቲክ ፊልድ በ10 ሲንቲ ሜትር ከፍታ የሚጓዝ ነው ተብሏል፡፡
ከዚህ በፊት የአለማችንን የፈጣን ባቡር ክብረወሰን ይዞ የነበረው፣ ሌላ የኩባንያው ምርት የሆነ ባቡር እንደነበረ ያስታወሰው ዘገባው፣ ይሄው ባቡር ከ12 አመታት በፊት በሰዓት 581 ኪሎሜትር ፍጥነት ተጉዞ እንደነበር ገልጧል፡፡
በአሁኑ ሰዓት አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኘው የአለማችን ፈጣን ባቡር በቻይና የተሰራና በሰዓት 431 ኪሎሜትሮችን የመጓዝ አቅም ያለው ነው፡፡

Read 1812 times