Saturday, 02 May 2015 10:34

ህገ ወጥ ሰው አዘዋዋሪዎችን ለመቅጣት አዲስ ህግ እየተዘጋጀ ነው

Written by  አለማየሁ አንበሴ
Rate this item
(15 votes)

      መንግስት አለማቀፍ ህገ ወጥ ሰው አዘዋዋሪ ደላላዎችን ለመቅጣት የሚያስችል አዲስ ህግ እያረቀቀ መሆኑን ምንጮች ጠቁመዋል፡፡ ህገ ወጥ የሰዎች ዝውውር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ በመሆኑ በእንቅስቃሴ የሚሳተፉ አካላትን ከወንጀለኛ መቅጫ ህጉ በተሻለ የሚያስቀጣ የህግ ረቂቅ በፍትህ ሚኒስቴር ተዘጋጅቶ በቅርቡ ይጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
“ህጉን ማውጣት ያስፈለገው በድርጊቱ የሚሳተፉ አካላትን እስካሁን በማስቀጣት የሚወሰዱት እርምጃዎች አርኪ ባለመሆናቸው ነው” ያሉት የፍትህ ሚኒስትሩ አቶ ጌታቸው አምባዬ፤ “ህገ ወጥ የሰው አዘዋዋሪ ደላላዎች ለኢትዮጵያውያን ስደት መባባስ ተጠያቂዎች ናቸው” ብለዋል፡፡
አሁን በስራ ላይ ያለው ህግ በዚህ ወንጀል ተሳታፊ የሆኑ ግለሰቦችን እስከ 20 ከመቶ እስራት የሚያስቀጣ ሲሆን አዲስ የሚረቀቀው ህግ የተሻሉ የቅጣት እርከኖች ይኖሩታል ተብሎ እንደሚጠበቅ አቶ ጌታቸው ገልጸዋል፡፡
በቅርቡ በሊቢያ አይኤስ (ዳኢሽ) የተሰኘው የሽብር ቡድን 30 ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን በአሰቃቂ ሁኔታ መግደሉን ተከትሎ መንግስት በዋናነት ህገ ወጥ ደላሎችን ተጠያቂ ያደረገ ሲሆን እርምጃ እንደሚወስድም መግለፁ ይታወሳል፡፡

Read 4711 times