Saturday, 02 May 2015 10:27

ንግድ ባንክ ከምስራቅ አፍሪካ ረጅሙን ህንጻ ሊያስገነባ ነው

Written by 
Rate this item
(10 votes)

198 ሜትር ይረዝማል፣ 46 ወለሎች ይኖሩታል

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከምስራቅ አፍሪካ አገራት በእርዝማኔው ቀዳሚ እንደሚሆን የተነገረለትን ሰማይ ጠቀስ ህንጻ በአዲስ አበባ ከተማ ለማስገንባት ከቻይናው የኮንስትራክሽን ኩባንያ (ሲኤስሲኢሲ) ጋር ስምምነት መፈጸሙን ዥንዋ ዘገበ፡፡
ባለፈው ማክሰኞ በአዲስ አበባ በተከናወነው የፊርማ ስነስርዓት ላይ ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ በቃሉ ዘለቀ፣ 198 ሜትር ርዝመትና 46 ወለሎች የሚኖረው የወደፊቱ የባንኩ ዋና ጽ/ቤት፣ በእርዝማኔው ብቻ ሳይሆን በአጠቃላይ ጥራቱም ከአፍሪካ ምርጥ ህንጻዎች አንዱ እንደሚሆን እናምናለን ብለዋል፡፡
ህንጻውን የሚገነባው የቻይናው የኮንስትራክሽን ኩባንያ ሲኤስሲኢሲ የኢትዮጵያ ቅርንቻፍ ጄኔራል ማናጀር ሶንግ ሱዶንግ በበኩላቸው፣ ኩባንያው በቻይና መሰል ግዙፍ የህንጻ ግንባታ ፕሮጀክቶችን በስኬታማ ሁኔታ ሲያከናውን እንደቆየ አስታውሰው፣ ህንጻው ለቻይና እና ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለምስራቅ አፍሪካም አዲስ ገጽታን የሚያላብስ እንደሚሆን ያላቸውን እምነት ገልጸዋል፡፡
ኩባንያውና ባንኩ በቀጣይ በጋራ ተረባርበው ፕሮጀክቱን ስኬታማ በማድረግ የጋራ ተጠቃሚነታቸውን እንደሚያረጋግጡም ገልጸዋል፡፡

Read 5300 times