Saturday, 02 May 2015 10:17

የኢትዮጵያ ሴቶች ማህበራት ቅንጅት በSMS ሎተሪ ጀመረ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

    የኢትዮጵያ ሴቶች ማህበራት ቅንጅት ባለፈው ዓመት ሐምሌ መጨረሻ ላይ ጀምሮ ያቋረጠውን 8400 አጭር የፅሁፍ መልዕክት ሎተሪ (SMS) ከነገ አንስቶ እንደሚቀጥል አስታወቀ፡፡
ሎተሪው በየቀኑ የሚበረከቱ የሳምሰንግ ሞባይሎች፣ በየሳምንቱ የሚበረከቱ ቶሺባ ላፕቶፖችና 21 ፍላት ስክሪን ቲቪዎች ሲኖሩት፣ በየ15 ቀኑ የሚወጡ የልብስ ማጠቢያ ማሽኖች፣ ሞተር ሳይክሎችና ፍሪጆች እንዳሉት ማህበሩ አስታውቋል፡፡ በሎተሪው መሃልና መጨረሻ ላይ የሚወጡ መኪኖችም እንደተዘጋጁ ለማወቅ ተችሏል፡፡
ከሎተሪው ሽያጭ የሚገኘው ገቢ በቀጥታ ማህበሩ ለጀመረው የኢ.ሴ ማዕከል ማሰሪያ የሚውል ሲሆን ማዕከሉ ለስብሰባዎችና ስልጠናዎች የሚያገለግሉ አዳራሾች፣ የቢሮ ክፍሎች፣ የሚከራዩ አዳራሾች ይኖሩታል ተብሏል፡፡ ከኪራይ የሚገኘው ገቢ ለጥቃት ሰለባዎችና በኢኮኖሚ አቅማቸው ዝቅተኛ ለሆኑ ሴቶች ድጋፍ ማድረግያ እንዲሁም ማህበሩ በገንዘብ ራሱን እንዲችል ያግዛል ተብሏል፡፡
ባለፈው ዓመት ሐምሌ መጨረሻ ላይ የተጀመረው የማህበሩ 8400 አጭር የፅሁፍ መልዕክት ሎተሪ ከ15 ቀናት በኋላ የተቋረጠው የ8100 የህዳሴ ግድብ SMS ሎተሪ በመጀመሩና ሁለቱን መልዕክቶች በአንዴ ማስተላለፍ ስለማይቻል ነበር ያለው ማህበሩ፤ ከነገ አንስቶ የሚጀመረው የ8400 አጭር የፅሁፍ መልዕክት ሎተሪ ለ3 ወራት ይቀጥላል ብሏል፡፡

Read 2865 times