Monday, 20 April 2015 14:07

ዳሳኒ የጎዳና ላይ ሩጫ ምዝገባ ሰጣ ዕድሎችም እንደተዘጋጁ ታውቋል፡፡

Written by 
Rate this item
(4 votes)

ከፍተኛ የገንዘብ ሽልማት ተዘጋጅቷል
ዕጣ የደረሰው በዱባይ የንግድ ትርኢት ይሳተፋል

ታላቱ ሩጫ በኢትዮጵያ ከኢስት አፍሪካ ቦትሊንግ ኩባንያ (ኮካኮላ) ጋር በመተባበር ከ2003 ዓ.ም ጀምሮ ሲያካሂድ የነበረውን የኮካኮላ የጎዳና ላይ ውድድር በ “ዳሳኒ የጎዳና ሩጫ” መተካቱን አስታወቀ፡፡ በቅርቡ በሚካሄድ የጐዳና ሩጫ ላይ ላሸነፉ ከፍተኛ የገንዘብ ሽልማት ተዘጋጅቷል ተብሏል፡፡
የሩጫው አዘጋጆች ከትናንት በስቲያ በሰጡት መግለጫ፤ ዳሳኒ ውሃ ዓለም አቀፍ የጥራት ደረጃ ያለው የኮካኮላ ምርት መሆኑን ጠቅሰው፣ ውድድሩ ከስም ለውጥ በስተቀር አራት ዓመት ሲካሄድ ከቆየው ውድድር ጋር ተመሳሳይ መሆኑን ገልፀዋል፡፡
ከዚህ ቀደም ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ 15ሺህ ተሳታፊዎች የተሳተፉበት ትልቅ የጐዳና ላይ ውድድር ማካሄዱን ጠቅሰው ዘንድሮ በሁለቱም ፆታ በሚካሄደው ውድድር 18ሺ ያህል ራጮች ይሳተፋሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ተናግረዋል፡፡
በመጪው ሰኔ 7 በዳያስፖራ አደባባይ ለሚካሄደው ውድድር ሰኞ ሚያዝያ 12 ቀን ምዝገባ እንደሚጀመር ጠቅሰው ሩጫውም 7.5 ኪ.ሜ ለጤና ሯጮች፣ 15 ኪ.ሜ ደግሞ ለአትሌቶች እንደሚሸፍን የተገለፀ ሲሆን አሸናፊዎች እስካሁን በኢትዮጵያ ታሪክ ለሯጮች ተሰጥቶ የማያውቅ የገንዘብና የቁሳቁስ ሽልማት እንደሚሸለሙ አስታውቀዋል፡፡
በወንድና በሴት ምድብ ተከፍሎ በሚካሄደው ውድድር፤ ከ1ኛ እስከ 10ኛ ለሚወጡ ተወዳዳሪዎች 285 ሺህ ብር የተዘጋጀ ሲሆን በሁለቱም ፆታ 1ኛ የሚወጣ 60ሺ ብር፣ 2ኛ 30 ሺህ ብር፣ 3ኛ 20,500 ብር እንደሚሸለም ታውቋል፡፡ በውድድሩ ለሚሳተፉ ተወዳዳሪዎች በ2008 በዱባይ በሚካሄደው የንግድ ትርዒት ለመሳተፍ የሚያስችል የዕጣ ዕድሎች የተዘጋጁ ሲሆን ዕጣው የደረሰው ተወዳዳሪ የደርሶ መልስ ቲኬትና የሁለት ቀን ወጪ እንደሚሸፈንለት ተጠቁሟል፡፡ የላፕቶፕና የሞባይል ቀፎ ዕጣ ዕድሎችም እንደተዘጋጁ ታውቋል፡፡

Read 1684 times