Tuesday, 14 April 2015 11:26

የየአገሩ አባባል

Written by 
Rate this item
(8 votes)

 የአይሁዶች አባባል
ሰው ሲያቅድ እግዚአብሔር ይስቃል፡፡
እናት፤ ልጅ ሳይናገር ይገባታል፡፡
ሃጢዓትን ሁለቴ ከፈፀምከው ወንጀል አይመስልም፡፡
ፍየልን ከፊት ለፊት፣ ፈረስን ከኋላ፣ ሞኝን በየትኛው በኩል አትጠጋቸው፡፡
ብልህነትህን በተግባር እንጂ በቃላት አታሳይ፡፡
ሻማ ለመግዛት ፀሃይን አትሽጥ፡፡
እግዚአብሔር ሸክምን ሲሰጥ ትከሻም አብሮ ይሰጣል፡፡
እግዚአብሔር ሁሉም ቦታ ሊሆን ስለማይችል እናቶችን ፈጠረ፡፡
ለጎረቤቱ የሚፀልይ ለራሱ ይደርስለታል፡፡
ልዕልት ማግኘት የምትሻ ከሆነ ራስህን ልዑል አድርግ፡፡
እግር የሌለው ሰው እስከማገኝ ድረስ ጫማ የለኝም ብዬ አዝን ነበር፡፡
በዓይንህ ያላየኸውን በአፍህ አትመስክር፡፡
ሳሙና ሰውነትን እንደሚያጥበው ሁሉ እንባም ነፍስን ያጥባል፡፡
አባት ለልጁ ሲሰጥ ሁለቱም ይስቃሉ፤ ልጅ ለአባቱ ሲሰጥ ሁለቱም ያለቅሳሉ፡፡

Read 1876 times