Tuesday, 14 April 2015 08:36

አዋሽ ወይን “ገበታ” የተሰኘ አዲስ ወይን ጠጅ አቀረበ

Written by 
Rate this item
(3 votes)

ሬስቶራንቶችን በክትፎ፣ ቁርጥና ጥብስ ያወዳድራል
አዋሽ ወይን ፋብሪካ ዘመናዊና ጥንታዊ የአጠማመቅ ዘዴዎችን በመጠቀም “ገበታ” የተሰኘ አዲስና ልዩ የወይን ጠጅ ምርት ለፋሲካ በዓል ማቅረቡን አስታወቀ፡፡
“ገበታ” የሚል ስያሜ የተሰጠው አዲሱ የአዋሽ ምርት ቀይና ነጭ ዘመናይ ወይኖች እንዳሉት ታውቋል፡፡ በሌላ በኩል የከተማዋ ሬስቶራንቶች በምርጥ ክትፎ፣ ቁርጥና ጥብስ ብቃታቸውን የሚያሳዩበት “የአዲስ ምርጥ ሥጋ ውድድር” ማዘጋጀቱን አዋሽ ወይን ለአዲስ አድማስ በላከው መግለጫ ጠቁሟል፡፡
በውድድሩ፤ የአዋሽ አዲስ ምርትን ለማስተዋወቅ እንደሚጠቀምበትም ጠቅሶ ሬስቶራንቶች በክትፎ፣ በቁርጥ፣ በጥብስ ወይም በአንዱ አሊያም በሁለቱም መወዳደር ይችላሉ ተብሏል፡፡
ውድድሩ፣ ደንበኞች በስልክ መልዕክት በሚያደርጉት ምርጫ (ክትፎ፣ ቁርጥ፣ ጥብስ) የሚወሰን ሲሆን ሬስቶራንቶች የመጀመሪያዎቹ 100 ውስጥ ከገቡ በየሳምንቱ እንደሚገለፅላቸው ታውቋል፡፡ ውድድሩ ከሚያዝያ 5-25 ድረስ ለሦስት ሳምንት የሚካሄድ ሲሆን በሶስተኛው ሳምንት መጨረሻ ላይ 50ዎቹ ውስጥ የገቡ ሬስቶራንቶች አዲስ አበባ ውስጥ ከሚገኙት ክትፎ፣ ቁርጥና ጥብስ አቅራቢ ሬስቶራንቶች ውስጥ በደንበኞች የተመረጡና ምርጥ መሆናቸውን የሚያሳይ ልዩ ሽልማት ይቀበላሉ ተብሏል፡፡ በእያንዳዱ ውድድር ከ1-5 የሚወጡ ሬስቶራንቶች አዋሽ በሚሰጣቸው ነፃ ወይን ጠጅ የቅምሻ ዝግጅት እንደሚያካሂዱ ተገልጿል፡፡  

Read 3571 times