Saturday, 28 March 2015 10:01

የጌትሽ ማሞ “ትወደኛለች” አዲስ አልበም ረቡዕ ይለቀቃል

Written by  ናፍቆት ዮሴፍ
Rate this item
(4 votes)

የድምፃዊና ግጥምና ዜማ ደራሲ ጌትሽ ማሞ “ትወደኛለች” የተሰኘ ሁለተኛው የሙዚቃ አልበም የፊታችን ረቡዕ እንደሚለቀቅ ተገለፀ፡፡ የዛሬ 6 ዓመት ባወጣው “እያሴ” የተሰኘ የመጀመሪያ አልበሙና “መብቴ መብቴ ነው” በሚል ተወዳጅ ነጠላ ዜማው የሚታወቀው ድምፃዊው፣ በአዲሱ አልበሙ 16 ዘፈኖችን ያካተተ ሲሆን ከአንዱ ዘፈኑ በስተቀር የቀሪዎቹን 15 ዘፈኖች ግጥምና ዜማ ራሱ እንደሰራ ለማወቅ ተችሏል፡፡ ሙዚቃውን በማቀናበር ሰለሞን ሃ/ማሪያም፣ ካሙዙ ካሳ፣ ሚካኤል ሃይሉ፣ ሚካኤል መለሰና ማሩ አለማየሁ እንደተሳተፉበትም ተገልጿል፡፡ ድምፃዊ ጌትሽ ማሞ ለተለያዩ አንጋፋና ወጣት ድምፃውያን ግጥምና ዜማ በመስጠት ይታወቃል፡፡

Read 2319 times