Saturday, 28 March 2015 10:00

“ውስጣዊ ግለት እና እንፋሎት” የስዕል ትርኢት ይከፈታል

Written by  ናፍቆት ዮሴፍ
Rate this item
(0 votes)

   ጋለሪያ ቶሞካ 14ኛውን የስዕል ትርዒት “ውስጣዊ ግለትና እንፋሎት” በሚል ርዕስ የፊታችን አርብ ከምሽቱ 12 ሰዓት ሳር ቤት ካናዳ ኤምባሲ ፊት ለፊት በሚገኘው ቤተ ስዕል እንደሚከፍት ተገለፀ፡፡ በዚህ ትርኢት የወጣቱ ሰዓሊ አሸናፊ መስቲካ ከ35 በላይ ስራዎች ለዕይታ እንደሚቀርቡ የጋለሪው ማኔጂንግ ዳይሬክተር ጋዜጠኛ ነብዩ ግርማ አስታውቋል። ሰዓሊው ዓለም በተቃርኖ የተሞላች መሆኗንና አንድ ሰው ከውጭ የሚያሳየው እያንዳንዱ እንቅስቃሴ በውስጡ ምን ሊመስል እንደሚችል የተረዳውን እሳቤ በስራዎቹ ለማንፀባረቅ ሞክሯል ተብሏል፡፡
የስዕል ትርኢቱ ለሁለት ወራት ለህዝብ ክፍት ሆኖ የሚቆይ ሲሆን ሚያዚያ 25 ከረፋዱ አራት ሰዓት ጀምሮ በሰዓሊው የአሳሳል ጥበብ፣ ፍልስፍና እና ለእይታ በቀረቡት ስዕሎቹ ዙሪያ ውይይት እንደሚካሄድ የጋለሪያ ቶሞካ አርት ዳይሬክተር ሰዓሊ እሸቱ ጥሩነህ ለአዲስ አድማስ ተናግረዋል፡፡

Read 1537 times