የተነሳህ ለት
የዛፍ ባላጋራ
ከምትተናነቅ
ከመቶ ቅርንጫፍ
ከሺህ ቅጠል ጋራ
እንደጡንቻ ሁሉ
ስልት በማፈርጠም
ወርደህ ከግንዱ ጋር
አንድ ለአንድ ግጠም፡፡
ሠም እና ሠም
አበባው አብቦ ንቡ ገብቶልህ
እንግዲህ ጎበሌ ማር ካላበላህ
“እንኳንስ ማርና አላየሁም ሰፈፍ”
እያልህ በመራራ ዜማ ከመንሰፍሰፍ
ያ! የቀፎው አውራ ማሩን የደበቀው
ንብ ሆኖ ሲመጣ ጭስ ሆነህ ጠብቀው፡፡
(“የአመድ ልጅ እሳት” የግጥም መድበል፤
መጋቢት 2007)
Published in
የግጥም ጥግ