Saturday, 21 March 2015 10:43

የየአገሩ አባባል

Written by 
Rate this item
(5 votes)

የተከፈተ አፍ ፆሙን አያድርም፡፡
ረዥሙም ዛፍ እንኳን እግሩ ስር የሚጠብቀው መጥረቢያ አለ፡፡
ሁሉም ድመት በጨለማ ጥቁር ነው፡፡
ሞኝ ሃብትን ሲያልም፤ ብልህ ደስታን ያልማል፡፡
የምግብ ፍላጎቱ የተከፈተለት ሰው፣ ማባያ አይፈልግም፡፡
ጥሩ ባልንጀራ ረዥሙን መንገድ ያሳጥራል፡፡
ልማድ ከብረት የተሰራ ሸሚዝ ነው፡፡
ባዶ ሆድ ጆሮ የለውም፡፡
ንዴት መጥፎ አማካሪ ነው፡፡
በአንዴ ሁለት አጋዘኖችን የሚያሳድድ ጅብ ፆሙን ያድራል፡፡
በእጅህ ዱላ ይዘህ ውሻን አትጥራ፡፡
የመፍትሄው አካል ካልሆንክ የችግሩ አካል ነህ፡፡
ሞኝ ሲረገም የተመረቀ ይመስለዋል፡፡
ከሰፈሩ ወጥቶ የማያውቅ ፣ እናቱ የባለሙያ ቁንጮ ትመስለዋለች፡፡
ታላላቆችን የሚያከብር ለራሱ ታላቅነት መንገዱን ይጠርጋል፡፡
ዓለም ለማንም ተስፋ (ቃል) አትሰጥም፡፡
ሌሊቱ ምን ቢረዝም መንጋቱ አይቀርም፡፡
ሳይወለድ ትችትን የሚፈራ ህፃን ጨርሶ አይወለድም፡፡
ከሴት ጋር ማውራት የማይወድ፣ ወንደላጤ ሆኖ ይቀራል፡፡
አባወራው መሬት ላይ የተቀመጠበት ቤት ውስጥ ወንበር እንዲሰጥህ አትጠብቅ፡፡
ወፍ በመመላለስ ብዛት ጎጆዋን ትሰራለች፡፡
የውሃውን ጥልቀት በሁለት እግሮቹ የሚለካ ሞኝ ብቻ ነው፡፡
የጅብ ዣንጥላ ይዞ የተመለሰ አዳኝን ስለአደኑ አትጠይቀው፡፡

Read 2197 times