ውሃን መጠጣት የምግብ ስልቀጣ ሂደትን ለማፋጠንና የሰመረ ለማድረግ እንዲሁም ቆዳን ለማጥራት፣ ድካምን ለማብረድና ትኩረት የመስጠት ችሎታን ለመጨመር ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ባለሙያዎች ይናገራሉ፡፡ ይሁን እንጂ ከልክ ሲያልፍ ለሞት እንደሚዳርግ የእንግሊዝ ተመራማሪዎች በቅርቡ ይፋ ያደረጉት መረጃ አመልክቷል፡፡
ከመጠን ያለፈ ውሃ መጠጣት የኩላሊትን የማጣራት ተግባር እንደሚያውክና ደማችንን በማቅጠን የሰውነታችንን የጨው ክምችት ቀንሶ ለሞት እንደሚዳርግ የጠቆመው መረጃው፤ የውሃው መጠን እጅግ ሲበዛ የአዕምሮአችን የውስጠኛው ክፍል እንዲያብጥና የአዕምሮ ስራ እንዲስተጓጎል ያደርጋል ብሏል፡፡ የደም ዝውውራችንንና ትንፋሻችንን የሚቆጣጠረው የአዕምሮአችን ክፍል በእብጠቱ ሳቢያ በሚደርስበት ጉዳት ስራው ሲስተጓጎል በትንፋሽ እጥረትና በደም ዝውውር መዛባት ምክንያት ለህልፈት ልናደርግ እንደምንችል መረጃው አመልክቷል፡፡
አንድ ሰው በየሁለት ሰዓቱ ከአንድ ጊዜ በላይ ሽንቱን ለመሽናት ወደመፀዳጃ ቤት ከተመላለሰና የሽንቱ ቀለም ንፁህ ውሃ የሚመስል ከሆነ፣ የጠጣው ውሃ ከመጠን ማለፉን እንደሚያመለክትም ተማራማሪዎቹ ይፋ ያደረጉት መረጃ ይጠቁማል፡፡
Published in
ዋናው ጤና
Latest from Administrator
- የእስራኤል እና የኢራን ፍጥጫ
- Insights on Israel's Response: Interview with Mr. Tomer Bar-Lavi, Chargé d’Affaires at the Embassy of Israel to Ethiopia
- Barr, a vocal Trump critic, says he will ‘support the Republican ticket’ in November
- Iran president warns of ‘massive’ response if Israel launches ‘tiniest invasion’
- "አልሞቷል" ፊልም ዛሬ በዓለም ሲኒማ ይመረቃል