Monday, 02 March 2015 10:53

“...ከእርግዝናጋር በተያየዘ የሚከሰት ጤናማ የሆነ ለውጥ...”

Written by 
Rate this item
(41 votes)

የእርግዝናዬን ግዜ ሳስበው እጅግ ይዘገንነኛል፡፡ ልጄ አሁን ሁለተኛ አመቱን ይዞአል፡፡ በባለቤቴም በኩል ይሁን በእኔ በኩል ያሉ ቤተሰቦች አንድ ልጅ መደገም እንዳለበት     ሲነግሩኝ...በሁኔታው ባምንም ...ሳስበው ግን እጅግ ይመረኛል፡፡ ከክብደት ጀምሮ ገጽታዬ በሙሉ እንዲሁም የቆዳ ቀለሜ የእኔ አልነበረም፡፡ ጭራሽ ነበር የተበለሻሸሁት፡፡ እኔነቴ     ተመልሶ ይመጣል የሚል እምነት አልነበረኝም፡፡ አሁን ደግሞ ተመልሼ ባረግዝ ...ልክ አንደበፊቱ ልበላሽ ነው ብዬ በጣም እጨነቃለሁ፡፡ ለመሆኑ ሐኪሞቹ ምን ይላሉ?
ይህን ጥያቄ ያቀረበችው እናት በእድሜዋ ወደ ሀያ አምስት አመት ስትሆን የምትኖረውም በአዲስ አበባ ነው፡፡ ስሙዋ ደግሞ ቆንጂት ብርሀኔ ይባላል፡፡ ዶ/ር ታደሰ ኡርጌ በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል የጽንስና ማህጸን ሕክምና እስፔሻሊስት በዚህ ዙሪያ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
በእርግዝና ወቅት በእያንዳንዱ የእናቶች የሰውነት ክፍል የሚከሰቱ ለውጦች ይኖራሉ፡፡ የሰውነት anatomic የምንለው ለውጥ ብቻ ሳይሆን በውስጣቸው የሚሰሩት ነገሮች በሙሉ የሚለወጡበት ሁኔታ ነው የሚኖረው፡፡ ይህም physiologic changes of pregnancy  ወይንም ከእርግዝናጋር በተያየዘ የሚከሰት ጤናማ የሆነ ለውጥ ማለት ነው፡፡ ይህ ለውጥ እንግዲህ በተለያዩ ሴቶች ላይ የሚኖረው ሁኔታ ይለያይ እንጂ ሁሉም ሴቶች ላይ የማይቀር ለውጥ ነው፡፡ በእያንዳንዱ የሰውነታችን ስርአት ውስጥ የተለያዩ ለውጦች ይካሄዳሉ፡፡ በዚህ ወቅት የሚታዩት አካላዊ ለውጦች በዋናነት ከኪሎ መጨመር ጋር ተያይዘው የሚመጡ ለውጦች ናቸው፡፡  ክብደት ሲጨምር የትኞቹ ክፍሎች ናቸው የሚለወጡት ያልን እንደሆን ሰውነት ውስጥ ከሚከማቸው ፈሳሽ ጀምሮ የሚወፍሩ አካላት ይኖራሉ፡፡ ልጅ እና የእንግዴ ልጅ ሌላውን ክፍል ይይዛል፡፡ የማህፀን እድገት የራሱን የሆነ ክፍል ይይዛል፣ የሽርት ውሀ የራሱ አስተዋፅኦ ይኖረዋል፡፡ ሌሎች ሰውነት ውስጥ የሚከማቹ  ስብን ጨምሮ የሰውነት ቅርፅ ለውጥ እንዲመጣ የሚያደርጉ ናቸው፡፡ እነኚህ ለውጦች ከምን የተነሳ ነው የሚመጡት ብለን ያየን እንደሆነ በዋናነት በእርግዝና ወቅት የሚቀየሩት ወይንም የእናቶች ሰውነት ውስጥ የሚመነጨው የሆርሞን መጠን ነው፡፡ ይህ የሆርሞን መጠን መጀመሪያ እርግዝናው እንደተከሰተ የዘር ፍሬ ከሚመረትበት ወይንም እንቁላሏ ከወጣችበት ቦታ የሚቀረው ክፍል Corpus luteum  ከምንለው የሚወጣው ነው የመጀመሪያው የሆርሞን ለውጥ፡፡ በመቀጠልም የእንግዴ ልጅ የሚያመነጨው እጅግ በጣም ብዙ የሆነ የሆርሞን መጠን ይኖራል፡፡ እነኚህ ሆርሞኖች በእርግዝና ወቅት ለሚከሰቱ ለውጦች ወይንም physiologic changes of pregnancy
ለምንለው ምንጭ ናቸው፡፡ ሰውነት ውስጥ ፈሳሽ እንዲከማች፣ ስብ እንዲከማች፣ ልጅ እንዲያድግ የጠቀስኳቸው አካላት በሙሉ እድገት እንዲያሳዩ የሚያደርጉት እነኚህ ሆርሞኖች ናቸው፡፡ ስለዚህ የለውጡ ምንጭ ከእርግዝናው ጋር የተያያዘ ነው፡፡
ከክብደት መጨመር በተጨማሪም ቆዳ ላይ የሚከሰቱ ለውጦች ይኖራሉ፡፡ ፊት ላይ፣ በእናቶች ሆድ ላይ፣ በጡት ላይ፣ የቆዳ (መልክ) መቀየር አይነት ሁኔታዎች ሊኖሩ ይችላሉ እና በተለያየ ቦታ በቆዳ ላይ የሚከሰቱ ለውጦች ይኖራሉ፡፡ እነኚህ  በቆዳ ላይ የሚታዩት ለውጦችም ቢሆኑ ከሆርሞኖች የተነሳ የሚመጡ ናቸው፡፡ አንዳንዶቹ እናቶች በሁለቱም ጎናቸው ላይ የመጥቆር አይነት ሁኔታ ይኖራል፡፡ mealasma ወይንም colasma  ወይንም mask of pregnancy የሚሉት ነገር ነው፡፡ ይህም ኢስትሮጂን የሚባለው ሆርሞን ሰውነት ውስጥ ከመብዛቱ የተነሳ ቆዳ ላይ የሚከሰተው ለውጥ ነው ማለት ነው፡፡ የእናቶችን ሆድ ደግሞ ያየን እንደሆነ መሀል ላይ የመጥቆር ሁኔታ ይኖራል፡፡ ይህም ከዛ ጋር የተያያዘ ነው  linea nigra  ነው የምንለው፡፡ ሌሎች ደግሞ ሸንተረሮች ይኖራሉ ሆድ፣ ጡት፣ እግር አካባቢ፣ እነኚህም ምንድነው በዋናነት የእነዚህ ሆርሞኖች መኖርና ሰውነት ክብደት እየጨመረ ሲሄድ ስብ እየተከማቸ ሲሄድ ወይንም ፈሳሽ እየተከማቸ ሲሄድ የመለጠጥና ከስር ያለው ቆዳ ወይም dermis የምንለው ቆዳ መሰነጣጠቅ ከዛም የመዳን ሁኔታዎች ናቸው እነኚህን ለውጦች የሚፈጥሩት ማለት ነው፡፡
አንዳንድ ግዜ ጤናማ ባልሆነ ሁኔታ ፈሳሽ ሰውነት ውስጥ የሚከማችበት ወይንም ከቆዳ ስር የሚከማችበት edema የምንለው ነገር ማለት ነው በብዛት የሚከማችበት ሁኔታ ሊኖር ይችላል፡፡ ይህ ጤነኛ ባልሆነ ሁኔታ ብዙዎቹ እናቶች ከሰማኒያ % በላይ የሚሆኑት ላይ edema የምንለው ነገር ሊኖር ይችላል፡፡ ግን በጣም ከልክ ያለፈ አይደለም፡፡ ከልክ ያለፈ የሚሆነው ጤነኛ ባላሆነ ሁኔታ በአንዳንድ ከእርግዝና ጋር ሊመጡ በሚችሉ ችግሮች ለምሳሌ በደም ግፊት የተነሳ በጣም ብዙ ፈሳሽ ከቆዳ ስር ሊከማች ይችላል፣ ሆዳቸው ላይም ሊከማች ይችላል፣ እግራቸው ላይ ሊሆን ይችላል፣ እጃቸው ሊያብጥ ይችላል፣ ፊታቸው ሊያብጥ ይችላል፡፡ እነኚህ ጤነኛ ባልሆነ ሁኔታ የተከሰቱ ሁኔታዎች ናቸው ፡፡ ግን normally ጤነኛም ሆኖ የአንዱ ክብደት መጨመርና የሰውነት ቅርፅ መለዋወጥ ዋናው ምክንያት የዚህ የፈሳሽ መጠራቀምና የስብ ሰውነት ውስጥ መከማቸት ሁኔታዎች ናቸው፡፡ እንግዲህ እነኚህ ሰውነት ውስጥ ከእንግዴ ልጅ በብዛት በሚመነጩ ቅመሞች ወይንም ሆርሞኖች የተነሳ የሚከሰቱ ናቸው ማለት ነው፡፡
ጥ/ በእርግዝና ግዜ የሚወሰድ ቫይታሚን ለክብደት መጨመርና ለቆዳ መበለሻሸት ምክንያት ይሆናልን?
መ/ እንግዲህ በአጠቃላይ በእርግዝና ወቅት የእናቶችን አመጋገብ ወይንም የምግብ ሁኔታ ያየን እንደሆን በተመጣጠነ ሁኔታ እናቶች ምግብ ማግኘት አለባቸው፡፡ ምግብ ስንል በዋናነት macronutrient  እና micronutrient  ብለን ነው የምንከፍላቸው፡፡ macronutrient
በዋናነት የምንመገባቸው ለሰውነት ግንባታና ለሀይል የሚያገለግሉ ምግቦች ናቸው፡፡ ይህ እንግዲህ ካርቦሀይድሬት፣ ፋት እና ፕሮቲን እያልን የምንጠራቸው ዋናዎቹ ምግቦች ናቸው ማለት ነው፡፡ ከዛ በተጨማሪ  micronutrient  የምንላቸው ቫይታሚንና ሚንራሎች ለሰውነት አስፈላጊ የሆኑ ንጥረ ነገሮች ናቸው፡፡ እነኚህ በዋናነት ጉልበት የመስጠትና ሰውነት መገንባት ቀጥተኛ የሆነ ተሳትፎ ባይኖራቸውም ሰውነት ውስጥ የሚካሄዱት የተለያዩ አይነት ሂደቶች በእነኚህ ሚንራሎችና ቫይታሚኖች በመታገዝ ነው፡፡ እነኚህ ለእናቲቱ ብቻ ሳይሆን እያደገ ላለው ፅንስ የሁለቱም የmacronutrient  እና  micronutrient  ምግቦች ምንጭ እናቲቱ ጋር ሲኖር ነው ወደ ልጁ ሊሄድ የሚችለው ማለት ነው፡፡ ስለዚህ የተመጣጠነ ምግብ የሚመገቡ እናቶች እነኚህ አስፈላጊ የሆኑት ንጥረ ነገሮች ከምግብ ውስጥ በቀን የሚያስፈልገውን ያክል ያገኛሉ ተብሎ ይታሰባል፡፡ ግን በቀን የሚያስፈልገውን ቫይታሚንና ፕሮቲን የምንላቸውን ንጥረ ነገሮች ከምግብ ውስጥ ብቻ የማይገኝባቸው ወይንም በቂ የማይሆኑበት ሁኔታዎች አሉ፡፡ አንዱ ምንድነው ምግባችን እነዛን ሚንራሎች ወይንም ቫይታሚኖች በበቂ ሁኔታ ያልያዘ ሊሆን ይችላል፡፡ ቢይዝም እንኳን በእርግዝና ወቅት የበለጠ  እነዚህን ቫይታሚንና ሚንራል አይረንና ፎሊክ የምንላቸው ነገሮች አስፈላጊ ይሆናሉ፡፡ ስለዚህ እነኚህ አስፈላጊ ንጥረ ነገሮች ናቸው እንጂ ከሚፈጠሩት የሰውነት ለውጦች ጋር በምንም መንገድ የማይገናኙ ናቸው፡፡ ቫይታሚኖቹና ሚንራሎቹ በእርግዝና ወቅት አስፈላጊ የሆኑ ንጥረ ነገሮች ናቸው፡፡ አንዲት እናት በትክክል ማግኘት የሚገባት ንጥረነገር ነው፡፡
    በእርግዝና ወቅት ያለው የአመጋገብ ሁኔታን በተመለከተ አንዲት እናት እርጉዝ ካልሆነችው እናት የበለጠ ምግብ መመገብ አለባት፡፡ በእርግዝና ወቅት የሰውነቷ የካሎሪ ፍላጎት ይጨምራል፡፡ ይህ የሚሆነው ለምንድነው? አንዱ ለሰውነት ግንባታ ነው፣ ሁለተኛ ፅንሱ ጤናማ ሆኖ ለማደግ የሚያስፈልጉ ንጥረ ነገሮች የሚገኙት ከእናቲቱ በመሆኑ ነው፡፡ ስለዚህ metabolic rate  የምንለው ነገር በእግዝና ወቅት ይጨምራል፡፡ ስለዚህ በእርግዝና ወቅት አንዲት እናት ቀድሞ ከምትመገበው የበለጠ መመገብ አለባት፡፡ የሰውነቷም ፍላጎት እያደገ ያለውም ፅንስ ይህንን ነው የሚፈልገው፡፡ ስለዚህ በምግብ ደረጃ ያየን እንደሆነ አንዲት እናት በእርግዝናዋ ወቅት ቢያንስ አንድ ተጨማሪ ምግብ መመገብ አለባት ተብሎ ነው የሚታሰበው፡፡ ይህ እንግዲህ ምንድነው አንዲት እናት በእርግዝናዋ ወቅት ወደ 300/ ኪሎ ካሎሪ ተጨማሪ ምግብ ትፈልጋለች ማለት ነው፡፡ ስለዚህ የምግብ ፍላጎት መጨመሩ የመጀመሪያዎቹን ሶስት ወራት ይሄ የማቅለሽለሹ፣ የማስመለሱና ምግብ የማስጠላቱ ነገር ከመኖሩ በስተቀር በተለይ ሁለተኛው ግማሽ የእርግዝና ወቅት እነኝህ ፍላጎቶች እየጨመሩ የሚሄዱበት ሁኔታ ነው ያለው፡፡ ስለዚህ ይሄ ጤናማ የሆነው በእርግዝና ወቅት የሚኖረው የምግብም ሆነ የካሎሪ ወይንም የጉልበት መጠን ፍላጎት የሚጨምርበት ወቅት ነው ማለት ነው፡፡ ይህ በእርግዝና ወቅት ሲሆን የምታጠባ እናት ደግሞ የምትፈልገው የምግብ ወይንም የጉልበት ወይንም የካሎሪ መጠን ከእርጉዝ ሴት በተሻለ ነው፡፡ ይህም አንዲት የምታጠባ እናት ወደ 500/ ኪሎ ካሎሪ ተጨማሪ ምግብ የምትፈለፍግበት ሁኔታ ነው ያለው፡፡ ስለዚህ ይህ በምግብ ሲሰላ ድሮ ከምትመገበው ሁለት ተጨማሪ ምግብ መመገብ አለባት፡፡ ስለዚህ ይሄ ለውጥ ከቫይታሚኖቹ የተነሳ አይደለም፡፡ በእርግጥ ቫይታሚኖች ሰውነታችን ውስጥ እያንዳንዱን metabolism የምንለውን ነገር የማመቻቸት ወይም facilitate የማድረግ ጠቀሜታ ነው ያላቸው፡፡
እያንዳንዱ ሰው የሚያመጣው ለውጥ ሊለያይ ይችላል፡፡ ግን በሰውነት ውስጥ የሚፈጠሩት ሆርሞኖች ለእነኚህ ልዩነቶች ወይም ለእነኚህ ለውጦች ዋናዎቹ ምክንያቶች ናቸው፡፡ ለምን አንዳንድ እርጉዝ ሴቶች ይህን ቀለም ያዙ? ለምን ሌሎቹ ይህን አልያዙም? ለሚለው ይህ በተለያዩ ምክንያቶች ሊሆን ይችላል፡፡ ለምሳሌ በአንፃራዊነት የእነኚህ ሆርሞኖች መጠን ምን ያክል ነው? በተጓዳኝ በእርግዝና ወቅት የሚመነጩ ሌሎች ነገሮች ይኖራሉ ወይ? አንዲት እናት ቆዳዋ ለፀሀይ ብርሀን ያለው sensitivity  ምን ያህል ነው? የሚሉት ነገሮች ይኖራሉ፡፡ melanosite  የምንላቸው ወይም የቆዳ ቀለምን ሊያመነጩ የሚችሉ ህዋሶች ምላሻቸው ምንድነው? ይህ በተለያዩ ምክንያቶች ሊለያይ ይችላል፡፡ ለምሳሌ እንዳንድ እናቶች ፊታቸው ላይ የመጥቆር ሁኔታ ይኖራል አንዳንዶቹ ምንም አይነት ለውጥ አይኖራቸውም፡፡ በእርግዝና ብቻም ሳይሆን አንዳንድ የወሊድ መቆጣጠሪያ መድኒት የሚወስዱ እናቶች ፊታቸው ላይ የመጥቆር ሁኔታ ሊፈጠር ይችላል ፡፡ አንዳንዶቹ ላይ ምንም ላይፈጠር ይችላል፡፡ ይህ የሚያሳየው በዋናነት ሆርሞኖቹ ተፅእኖ ቢኖራቸውም ሆርሞኖቹ ብቻቸውን ሳይሆን ሌሎች ተጓዳኝ ወይም ያንን ነገር ሊገልፁ የሚችሉ ከ genetic ከመሳሰሉት environmental factors
ሊሆን ይችላል፡፡ የለውጦቹ ዋና ምንጮች ሆርሞኖቹ ቢሆኑም ለውጡ ግን እንደየ ሰዉ ሊለያይ ይችላል፡፡




Read 38705 times