Monday, 02 March 2015 08:52

800 ወጣቶች የነፃ ትምህርት ዕድል ተጠቃሚ ይሆናሉ

Written by 
Rate this item
(2 votes)

በአስር አመት ውስጥ የኢኮኖሚ አቅማቸው ደካማ ለሆኑ 800 ወንድና ሴት ተማሪዎች የነፃ ትምህርት ዕድል የሚያስገኘው የማስተር ካርድ ስኮላር ፕሮግራም ትናንት በይፋ ተጀመረ፡፡ በ100 ወጣት ወንድና ሴት ተማሪዎች የተጀመረው የነፃ ትምህርት ዕድል፤ከዘጠነኛ እስከ አስራ ሁለተኛ ክፍል ድረስ ትምህርታቸውን ለሚከታተሉ  ተማሪዎች ድጋፍ ያደርጋል፡፡ የኢኮኖሚ አቅማቸው ደካማ ሆኖ ጥሩ የትምህርት ፍላጐት ያላቸውንና ጐበዝ ተማሪዎችን ከአማራ፣ ከኦሮሚያ፣ ከደቡብ ክልሎችና ከአዲስ አበባ አስተዳደር በማሰባሰብ የነፃ ትምህርት ዕድሉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ የተደረገው ተብሏል፡፡  
Forum for African women education (FAWE) በተባለው ድርጅት በተጀመረው የነጻ ትምህርት እድል ፕሮጀክት በአስር ዓመት ውስጥ ተጠቃሚ የሚሆኑት 800 ወጣቶች ሲሆኑ 600 ያህሉ ሴት ተማሪዎች ናቸው፡፡ በትምህርታቸው የላቀ ውጤት የሚያስመዘግቡ ተማሪዎች በውጭ አገር ነጻ የከፍተኛ ትምህርት ዕድል ሊያጋጥማቸው እንደሚችልም ተገልጿል፡፡

Read 1783 times