Saturday, 14 February 2015 16:02

በአለማችን የስዕል ሽያጭ ታሪክ ክብረ ወሰን ተመዘገበ

Written by 
Rate this item
(3 votes)

አንድ ስዕል 300 ሚሊዮን ዶላር ተሽጧል
የኳታሩ ሚ/ር ከ1 ቢሊዮን ዶላር በላይ የመንግስት በጀት ለስዕል ግዢ አውጥተዋል

በፈረንሳዊው ሰዓሊ ፖል ጎጊን እ.ኤ.አ በ1892 የተሳለውና “ናፊያ ፋ ልፖኢፖ” የሚል ርዕስ ያለው ስዕል በአለማችን የስዕል ስራዎች ሽያጭ ታሪክ ክብረ ወሰን ባሰመዘገበ መልኩ በ300 ሚሊዮን ዶላር መሸጡን ኒውዮርክ ታይምስ ዘገበ፡፡
የሁለት ልጃገረዶችን ምስል የሚያሳየው ይህ ስዕል፣ ሩዶልፍ ስቴችሊን በተባሉት ስዊዘርላንዳዊ የስነጥበብ ስራዎች ሰብሳቢ ግለሰብ ባለቤትነት ኩንስት በተባለ ሙዚየም ውስጥ ለረጅም አመታት እንደቆየና ሰሞኑን በኳታር ለሚገኝ አንድ ሙዚየም እንደተሸጠ ዘገባው ጠቅሷል፡፡
በስቴችሊንና በኩንስት ሙዚየም መካከል በቅርቡ አለመግባባት መፈጠሩን ተከትሎ፣ ግለሰቡ ስዕሉን ለኳታሩ ሙዚየም ለመሸጥ መወሰናቸውን ያስታወሰው ዘገባው፣ ኳታር ከዚህ ቀደምም በስዕል ሽያጭ ታሪክ ከፍተኛው ገንዘብ የተከፈለበትንና በሰዓሊ ፖል ሴዛኔ የተሳለውን የስዕል ስራ በ158 ሚሊዮን ፓውንድ መግዛቷን አክሎ ገልጧል፡፡
ኳታር ለስነጥበብ ስራዎች ግዢ ከፍተኛ ገንዘብ እንደምታወጣና፣ ባለፈው አመት ከዚህ አለም በሞት የተለዩት የቀድሞው የኳታር የባህል ሚኒስትር ሼክ ሳኡድ ቢን ሞሃመድ አል ጣኒ፣ ከ1 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገንዘብ ከመንግስት ካዝና ወጪ በማድረግ ለስነጥበብ ስራዎች ግዢ ማዋላቸውንም አስታውሷል፡፡


Read 3196 times