በሌላ በኩል ጭብጡን በፈረስ ዙሪያ ያደረገና ርእስ ያልተሰጠው የሥእል አውደርእይ በአሊያንስ ኢትዮ-ፍራንስ ባለፈው ሰኞ እንደተከፈተ ለማወቅ ተችሏል፡፡ እስከ ጥር 18 ቀን 2004 ዓ.ም በሚቆየው በዚሁ አውደርእይ የሠዓሊ ሙሉ ቀን ደበበ 23 ፈረስ ነክ የቀለም ቅብ ሥራዎችና 6 የንድፍ ሥራዎች ቀርበዋል፡፡ ሠዐሊው ካሁን ቀደም በርካታ ጊዜ በቡድን አውደርእይ ያቀረበ ሲሆን ለብቻው ሲያቀርብ ግን ይህ የመጀመሪያው ነው፡፡ በሌላም በኩል 80 ያህል የወርቅነህ በዙ ሥራዎችን ያካተተ የስዕል አውደርዕይ በአበሻ አርት ስቱዲዮና አዲስ ምዕራፍ ፕሮሞሽን ትናንት ተከፈተ፡፡