Saturday, 07 February 2015 13:57

የእንግሊዙ ፓርቲ ለፌስቡክ በአመት ከ1 ሚ ፓውንድ በላይ ያወጣል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ብዙ ወጣቶች በምርጫ ድምጽ እንዲሰጡት ለማድረግ ነው
የእንግሊዙ ጠቅላይ ሚኒስትር ዴቪድ ካሜሩን አባል የሆኑበት ወግ አጥባቂው ትሮይ ፓርቲ በቅርቡ በሚከናወነው ምርጫ ብዙ ድምጽ ለማግኘት በፌስቡክ ለሚያደርገው ቅስቀሳ በአመት ከ1 ሚሊዮን ፓውንድ በላይ ገንዘብ ወጪ እንደሚያደርግ ዘ ኢንዲፔንደንት ዘገበ፡፡
ፓርቲው ባለፈው አመት መስከረም ላይ ብቻ የፌስቡክ ተጠቃሚዎች እንዲወዱት ለማድረግ የከፈለውን 25 ሺህ ፓውንድ ጨምሮ፣ በወሩ በድምሩ 123ሺህ የእንግሊዝ ፓውንድ ለፌስቡክ ኩባንያ ገቢ ማድረጉን የጠቆመው ዘገባው፤ ባለፈው ህዳር ወር ፖለቲካዊ ይዘት ላለው ሌላ ድረገጽ 115 ሺህ ፓውንድ መክፈሉን አስታውቋል፡፡
ለፌስቡክ ይህንን ያህል ወጪ ማውጣቱን እንደ ትልቅ ኢንቨስትመንት እንደሚቆጥረው የገለጸው ትሮይ ፓርቲ፤ ገንዘቡን የሚያወጣው ቁጥራቸው የበዛ ወጣቶች በምርጫ ድምጻቸውን እንዲሰጡት በማሰብ እንደሆነ ቢገልጽም፣ የሚሳካለት አይመስልም ብሏል ዘገባው፡፡
በፌስቡክ ተጠቃሚዎች ዘንድ ተወዳጅነትን በማትረፍ ረገድ፣ ብሪቴን ፈርስት የተባለው ፓርቲ ትሮይን በእጥፍ ያህል እንደሚበልጠው የጠቀሰው ዘገባው፣  ብሪቴን ፈርስት 650 ሺህ፣ ትሮይ ደግሞ 340 ሺህ ያህል የፌስቡክ ወዳጆች እንዳሏቸው ጨምሮ ገልጧል፡፡




Read 1691 times