Saturday, 31 January 2015 13:12

የድምፅ ውድድሩ ዛሬ ይጠናቀቃል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

በአቢሲኒያ ኢንተርቴይንመንት እየተዘጋጀ በኤፍኤም 96.3 ላይ ሲሰራጭ የቆየው የቀጥታ የስልክ መስመር የድምፅ ውድድር ዛሬ ይጠናቀቃል፡፡
ለመጨረሻ ውድድር የቀረቡ አምስት ተወዳዳሪዎች በቀጥታ ከስቱዲዮ የሚያካሂዱትን የድምፅ ውድድር ለመዳኘት ታዋቂ የሙዚቃ አቀናባሪዎችና ድምፃውያን በስፍራው ይገኛሉ፡፡ በውድድሩ ከአንድ እስከ ሶስት የሚወጡት ተወዳዳሪዎች የግጥም፣ የዜማና የሙዚቃ ቅንብር ሙሉ ወጪያቸው ተችሎ ነጠላ ዜማ እንዲሰሩ እንደሚደረግ የፕሮግራሙ ዋና አዘጋጅ አቶ አባተ ማንደፍሮ ለአዲስ አድማስ ገልጿል፡፡
አቢሲኒያ ኢንተርቴይንመንት እስከ አሁን ድረስ በአምስት ዙሮች ባደረገው የቀጥታ ስልክ መስመር የድምጽ ውድድር በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ከ350 በላይ ጀማሪ ድምጻውያን እንደተካፈሉ አቶ አባተ ተናግሯል፡፡ ፕሮግራሙ የተጀመረበት 4ኛ ዓመት በዚሁ ዕለት እንደሚከበርም ገልጿል፡፡

Read 2231 times