በድምፃዊ ዳንኤል ዘውዱ የተሰራው “የዝና” የተሰኘና ነባር ዘፈኖች የተካተቱበት የሙዚቃ አልበም በገበያ ላይ ዋለ፡፡
በ1990ዎቹ መጀመሪያ ላይ ከዚህ ዓለም በሞት የተለየውን የተስፋዬ ወርቅነህን ተወዳጅ ዜማዎች ሪሚክስ በማድረግና በድጋሚ በመስራት በገበያ ላይ ያዋለው ድምፃዊ ዳንኤል ዘውዱ ለዘፈኖቹ ግጥምና ዜማ ደራሲዎች ተገቢውን ክፍያ መፈፀሙንና የቅጂ መብቱን ጠብቆ መስራቱን ለአዲስ አድማስ ገልጿል፡፡
የዘፈኖቹ ግጥሞች የተወሰነ ማሻሻያዎች እንደተደረጉባቸውና በታዋቂ የሙዚቃ አቀናባሪዎች መሰራታቸውንም ድምፃዊው ተናግሯል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና