Saturday, 24 January 2015 14:00

በሳኡዲ ውሻ አሰቃይተው የገደሉ የ5 አመት እስር ተፈረደባቸው

Written by 
Rate this item
(0 votes)

በሳኡዲ አረቢያ አንድን ውሻ በከፍተኛ ሁኔታ አሰቃይተው ገድለዋል በሚል ተከሰው ፍርድ ቤት የቀረቡ ሁለት ወጣቶች የ5 አመት እስር ወይም የ500 ሺህ የሳኡዲ ሪያል መቀጣታቸውን አረብ ኒውስ ዘገበ፡፡
ወጣቶቹ ከሳምንታት በፊት ውሻውን በከፍተኛ ሁኔታ ሲደበድቡና ሲያሰቃዩ ቆይተው ለሞት እንደዳረጉት የሚያሳየውና በአንደኛው ወጣት ሞባይል የተቀረጸው አስር ደቂቃ ያህል የሚረዝም የቪዲዮ ፊልም በማህበራዊ ድረገጾች አማካይነት በስፋት መሰራጨቱን ተከትሎ፣ ድርጊቱ ከፍተኛ ተቃውሞ ማስነሳቱን የጠቆመው ዘገባው፣ ፖሊስ ወንጀለኞቹን ተከታትሎ በቁጥጥር ስር ማዋሉን ገልጿል፡፡
ፖሊስ ወንጀለኞቹ መኪና እያሽከረከሩ ውሻውን በመሬት ላይ በመጎተት ሲያሰቃዩት እንደነበር በሚያሳየው በዚህ ቪዲዮ ላይ የታየውን የመኪናዋን ታርጋ ቁጥር በመመዝገብ የድርጊቱን ፈጻሚዎች ተከታትሎ በሪያድ በቁጥጥር ስር ማዋሉንም ዘገባው አስረድቷል፡፡
የአገሪቱ የግብርና ሚኒስትር ጃቢር አል ሸሪ፤ ወጣቶቹ በውሻው ላይ የማሰቃየት ወንጀል መፈጸማቸው በመረጋገጡ፣ በአገሪቱ ህግ እና የባህረ ሰላጤው አገራት ባወጡት እንስሳትን የማሰቃየት ወንጀል ህግ መሰረት፣ ፍርድ ቤት ቀርበው ቅጣት እንደተጣለባቸው አስታውቀዋል፡፡

Read 1618 times