Saturday, 24 January 2015 13:58

“ምስጋና” የኪነጥበብ ድግስና የስዕል አውደርዕይ ተከፈተ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

በእቴጌ ጣይቱ ሆቴል ላይ የደረሰውን የቃጠሎ አደጋ ለመታደግ በተደረገው ርብርብ ላይ ተሳታፊ ለነበሩ አካላት “ምስጋና” የሚቀርብበት ምስጋና የተሰኘ ልዩ የኪነ ጥበብ ዝግጅት በጣይቱ ሆቴል ግቢ ውስጥ ተከፈተ፡፡ ከጥር 14 እስከ ጥር 17 ቀን 2007 ዓ.ም ድረስ ይቆያል በተባለው በዚሁ የኪነ ጥበብ ፕሮግራም ላይ የተለያዩ ሰዓሊያን የስዕል ስራዎች ለዕይታ ቀርበዋል፡፡ ከስዕል ኤግዚቢሽኑ በተጨማሪ ልዩ የሰርከስ፣ የሙዚቃ ትርኢትና ሥነ ግጥሞች የሚቀርቡ ሲሆን ለህፃናት የታሪክ ነገራ እና የስዕል ስራዎች ስልጠናም እንደሚሰጥ አዘጋጆቹ ገልፀዋል፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ አቶ ገብረፃዲቅ ሀጎሽ ፕሮግራሙን መርቀው በከፈቱበት  ወቅት እንደተናገሩት፤ ታሪካዊውንና ጥንታዊውን ሆቴል ከቃጠሎው አደጋ ለመታደግና የህዝብ ሀብት የሆነውን ሆቴል  ለማዳን ህብረተሰቡ ያደረገውን ተጋድሎ እናደንቃለን ብለዋል፡፡ ሆቴሉ በቋሚነት የቀድሞ ይዘቱንና ታሪካዊነቱን በጠበቀ መንገድ እንዲታደስ የሚደረግበትን ሁኔታ ለማመቻቸት ጥረት በመደረግ ላይ መሆኑንና ሆቴሉን ከፀሐይና ከዝናብ ለመከላከል የሚያስችል ጊዜያዊ ጥገናው በሆቴል አስተዳደሩ መጀመሩን አመልክተዋል፡፡

Read 1640 times