እኤአ በ1995 በፊፋ የአለማችን ኮከብ እግር ኳስ ተጫዋች ተብሎ የተመረጠው ላይቤሪያዊ እግር ኳስ ተጫዋች ጆርጅ ዊሃ ሰሞኑን በተካሄደው የአገሪቱ የሴኔት ምርጫ ከፍተኛ ድምጽ በማግኜት አሸናፊ መሆኑን ቢቢሲ ዘገበ፡
በኢቦላ ወረርሽኝ ክፉኛ በተጎዳችዋ ላይቤሪያ ሰሞኑን በተካሄደው ምርጫ ሞንቴራዶ የተባለችውን ግዛት በመወከል የተወዳደረው ዊሃ፣ 78 በመቶ ድምጽ በማግኘት ማሸነፉን የጠቆመው ዘገባው፣ ግዛቲቱን ወክሎ የተወዳደረው ተፎካካሪው የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ኤለን ጆንሰን ሰርሊፍ ልጅ ሮበርት ሰርሊፍ 11 በመቶ ድምጽ በማግኜት መሸነፉን አስታውቋል፡፡በምርጫው ካሸነፉት ተወዳዳሪዎች መካከል የቀድሞው የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ቻርለስ ቴለር የቀድሞ የትዳር አጋር ጄዌል ሃዋርድ ቴለር አንዷ ናቸው፡፡
በ2005 በተካሄደው የአገሪቱ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ተወዳድሮ የነበረው ዊሃ፣ በኤለን ጆንሰን ሰርሊፍ መሸነፉን ዘገባው አስታውሷል፡፡
Published in
ከአለም ዙሪያ