Print this page
Monday, 08 December 2014 14:44

የፈረንሳይ ፕሬዚዳንት በኢቦላ የተጠቁ ሀገራትን ጐበኙ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

   የፈረንሳይ ፕሬዚዳንት ፍራንሲስ ኦላንዴ፤ በኢቦላ የተጠቁ የምዕራብ አፍሪካ ሃገራትን የጐበኙ ሲሆን ባለፈው አርብ እለት ጉብኝታቸውን የጀመሩት ከጊኒ ነበር፡፡
ፕሬዚዳንቱ 1200 ዜጐቿን በቫይረሱ ለተነጠቀችው ጊኒ፤ ቀደም ሲል በሀገራቸው መንግስት ስም 100 ሚሊዮን ዩሮ እንደለገሱና ገንዘቡም በአገሪቱ የኢቦላ ህክምና ማዕከላትን ለማቋቋም እንደዋለ ተዘግቧል፡፡ በአሁኑ ጉብኝታቸው 200 አልጋዎችንና የተንቀሳቃሽ ህክምና ማዕከል ድጋፍ እንዳደረጉ ታውቋል፡፡
ፕሬዚዳንቱ በጊኒ የተለያዩ የህክምና ጣቢያዎችን ተዘዋውረው የጐበኙ ሲሆን ከጤና ባለሙያዎችና ተመራማሪዎች ጋር በሽታውን በተመለከተ የጠረጴዛ ዙሪያ ውይይት ማድረጋቸውም ተጠቁሟል፡፡ በኢቦላ የተጠቁ የአፍሪካ ሀገራትን በመጐብኘት የመጀመሪያው የአውሮፓ መሪ ናቸው የተባሉት ፕሬዚዳንት ኦላንዴ፤ ከጊኒው ጉብኝታቸው በኋላ በኢቦላ ወደተጠቃችው ሌላኛዋ አፍሪካዊት ሀገር ወደ ሴኔጋል ተጉዘው የፈረንሳይኛ ተናጋሪ የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች ስብሰባ ላይ እንደተሳተፉ ተዘግቧል፡፡
በተመሳሳይም ከስብሰባው ጐን ለጐን በጊኒ እንዳደረጉት ሁሉ በኢቦላ ጉዳይ ከሴኔጋል የጤና ሚኒስትሮችና የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ጋር መክረዋል ተብሏል፡፡
ፕሬዚዳንት ኦላንዴ በሶስት ቀናት ቆይታቸው ከጊኒና ሴኔጋል በተጨማሪ ሴራሊዮንና ላይቤሪያን እንደጎበኙ ታውቋል፡፡  

Read 1553 times
Administrator

Latest from Administrator