Saturday, 29 November 2014 11:34

ራያ ቢራ ፋብሪካ የሙከራ ምርት ሊጀምር ነው

Written by  መታሰቢያ ካሳዬ
Rate this item
(1 Vote)

       ከአንድ ነጥብ አምስት ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባው የራያ ቢራ ምርት ለመጀመር የሚያስችል ሙከራ ለማድረግ በዝግጅት ላይ መሆኑ ተገለፀ፡፡600 ሚሊዮን ብር ከባለ አክስዮኖች በማሰባሰብና 910 ሚሊዮን ብር የባንክ ብድር በማስፈቀድ የተቋቋመው የራያ ቢራ አክስዮን ማህበር የፋብሪካ ተከላ ስራ፣ የመጥመቂያ ማሽኖች፣ ጋኖችና የጠርሙስና የድራፍት ቢራ የማሸግያ ማሽኖች ተከላ እንዲሁም ለምርት ግብአት የሚውሉ ኬሚካሎችና የተለያዩ ማሽኖችን በማስመጣት ፋብሪካው ለምርት ዝግጁ እንዲሆን መደረጉም ተገልጿል፡፡አክስዮን ማህበሩ ባለፈው እሮብ በኢሊሌ ሆቴል አዘጋጅቶት በነበረው የባለአክስዮኖች የሼር ሰርተፍኬት አሰጣጥ ሥነ-ስርዓት ላይ ዋና ሥራ አስኪያጁ አቶ አታክልት ኪሮስ እንደተናገሩት ፋብሪካው ምርቶቹን ለማምረት የሚያስችሉትን ግብአቶች በሙሉ በማሟላት ዝግጁ መደረጉንና በቅርቡም የሙከራ ምርት ማምረት እንደሚጀምር ተናግረዋል፡፡በአንድ አመት ጊዜ ውስጥ የፋብሪካ ግንባታውንና የማሽኖች ተከላ ስራውን በማጠናቀቅ ምርት ለማስጀመር የሚያስችል የደረቀና እርጥብ ሙከራ ለማድረግ ዝግጅት ላይ እንደሚገኙም ሥራ አስኪያጁ ገልፀዋል፡፡የራያ ቢራ አክሲዮን ማህበር 2441 አባላት ያሉት ሲሆን ሰሞኑን ለባለአክሲዮኖቹ የአክሲዮን ባለቤትነት ማረጋገጫ ሰርተፍኬት ሰጥቷል፡፡

Read 2302 times