Print this page
Saturday, 29 November 2014 11:33

የኢትዮጵያ ምርት ገበያ አዳዲስ ቅርንጫፎች ከፈተ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

የኢትዮጵያ ምርት ገበያ በትግራይ ክልል ሽራሮ ከተማና በአማራ ክልል አብርሃ ጅራ ከተማ አዳዲስ የምርት መቀበያ ቅርንጫፎችን መክፈቱን አስታወቀ፡፡
ሰሞኑን ተመርቆ  አገልግሎት መስጠት የጀመረው በትግራይ ክልል ሽራሮ የሚገኘው ቅርንጫፍ በፀለምቲ፣ አስገደ ፅምብላ፣ ታህታይ አድያቦ፣ ላዕላይ አድያቦ፣ መደባይ ዛና፣ ነአደር አዴት፣ መረብለኧ፣ ወኔለኧ፣ ቆላ ተምቤን፣ ጣንቋ አበርገሌ፣ ሰሀርቲ ሳምረ እና ወልቃይት አካባቢ የሚመረቱ ምርቶችን ለግብይት የሚያመቻች ነው ተብሏል፡፡ በተጨማሪም በአካባቢው ያሉ ሌሎች ወረዳዎችም ተጠቃሚ ይሆናሉ ተብሏል፡፡ በአማራ ክልል የሚከፈተው የአብርሃ ጅራ ቅርንጫፍ በምዕራባዊ አርማጭሆ በሚገኙት በአብርሃ ጅራ፣ አብደራፊ ኮርሁመር፣ ጐብላ፣ ግራር ውሃ፣ መሃሪሽ እና ዘመነ መሪኬ እንዲሁም በፀገዲ በሚገኙ አካባቢዎች የሚመረቱ ምርቶች የሚቀርቡበት ይሆናል ተብሏል፡፡
በምርት ገበያው አሠራር እነዚሁ ቅርንጫፎች እንደሌሎቹ ቅርንጫፎች ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም የምርት ናሙና በመውሰድ፣ ክብደትና ጥራት የሚለኩበት እንዲሁም አስተማማኝ የመጋዘን አገልግሎት የሚሰጡ ይሆናሉ፤ ለአርሶ አደሮቹም ዘመናዊና ቀልጣፋ አገልግሎት በመስጠት ለአገሪቱ ምርት ግብይት መሻሻል የጐላ አስተዋጽኦ ያበረክታሉ ተብሏል፡፡ ምርት ገበያው በአሁን ወቅት በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ የምርት ማስረከቢያ ማዕከላቱን ከ17 ወደ 19 ከፍ ማድረጉም ተጠቁሟል፡፡

Read 2252 times
Administrator

Latest from Administrator