Saturday, 22 November 2014 12:45

የሽብር ጥቃቶችና የሚያደርሱት የሞት አደጋ በከፍተኛ ደረጃ ጨምሯል

Written by 
Rate this item
(0 votes)
  • ዓምና  በተፈጸሙ 10 ሺህ ያህል ጥቃቶች፣ ከ18 ሺህ በላይ ሰዎች ሞተዋል
  • 6ሺህ 362 ሰዎች የሞቱባት ኢራቅ ቀዳሚነቱን ይዛለች

        በአለማችን የሚፈጸሙ የሽብር ጥቃቶች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ እያደገ በመምጣት አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱንና ባለፈው የፈረንጆች አመት ብቻ ከ18 ሺህ በላይ የተለያዩ አገራት ዜጎች ለህልፈት መዳረጋቸውን ስካይ ኒውስ ዘገበ፡፡
የአለማቀፉን የሽብርተኝነት አመልካች ጥናት ሪፖርት ጠቅሶ ዘገባው እንዳለው፣ እ.ኤ.አ በ2013 ብቻ በአለማችን የተለያዩ ክፍሎች 10ሺህ ያህል የሽብር ጥቃቶች የተፈጸሙ ሲሆን፣ በጥቃቶቹ የሞቱ ሰዎች ቁጥር ከአንድ አመት በፊት ከነበረው  በእጥፍ ያህል መጨመሩንም ጠቁሟል፡፡በአመቱ በሽብር ጥቃቶች በርካታ ዜጎች የሞቱባት ቀዳሚ የዓለማችን አገር ኢራቅ ስትሆን፣ በአገሪቱ 6ሺህ 362 ያህል ሰዎች ከሽብር ጥቃቶች ጋር በተያያዘ ለሞት ተዳርገዋል፡፡
ችግሩ በከፍተኛ ሁኔታ የተስፋፋበቸው ሌሎች የአለማችን አገራት አፍጋኒስታን፣ ፓኪስታን፣ ሶሪያና ናይጀሪያ ሲሆኑ፣ አይኤስ፣ አልቃይዳ፣ ታሊባንና ቦኮሃራም ደግሞ በአገራቱ አብዛኞቹን ጥቃቶች የፈጸሙ ቡድኖች ናቸው ተብሏል፡፡ የሽብርተኝነት እንቅስቃሴዎች በሚታዩባቸው 162 የአለማችን አገራት ላይ የሰራውን አለማቀፍ የሽብርተኝነት አመልካች ጥናት ለሁለተኛ ጊዜ ይፋ ያደረገው፣ ኢንስቲቲዩት ፎር ኢኮኖሚክስ ኤንድ ፒስ የተባለ አለማቀፍ ተቋም ነው፡፡

Read 3075 times