Print this page
Saturday, 22 November 2014 12:23

የውጭ ጉዞና የትምህርት ክፍያ ማረጋገጫ ዋስትና መስጠት ተጀመረ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ከአገር ውጭ የሚደረጉ ጉዞዎችንና የትምህርት ክፍያ ማረጋገጫ ዋስትናዎችን መስጠት እንደጀመረ የገለፀው ኢትዮ ለይፍ ኤንድ ጀነራል ኢንሹራንስ አክሲዮን ማህበር፤ ይህም አገልግሎቱን የተሟላ ለማድረግ እንደሚያስችለው የድርጅቱ ኃላፊዎች ከትናንት በስቲያ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አስታወቁ፡፡
በአገሪቱ የኢንሹራንስ ገበያ ውስጥ አዳዲስ አሠራሮች ናቸው ከተባሉት ከእነዚህ የመድን ዋስትናዎች በተጨማሪ የህክምና፣ የዕድሜ ልክ፣ የኢንዶውመንት፣ የብድር ዕዳ ማስወገጃ፣ የእሳት ቃጠሎና የመብረቅ፣ የአበባ እርሻ፣ የሠራተኞች ጉዳት ካሳ፣ የምሕንድስና መድንና ሌሎች የዋስትና ዓይነቶችንም ለአገልግሎት ማቅረቡን አስታውቋል፡፡
በጥቅምት ወር 2001 ዓ.ም ከብሔራዊ ባንክ በተሰጠው ፍቃድ መሰረት ሥራ የጀመረው አክስዮን ማህበሩ፤ በአሁኑ ወቅት 58ሺ አክሲዮኖችን ለሽያጭ ማቅረቡንና የአገልግሎት አድማሱን በማስፋት ሚሊዮኖችን ለማገልገል ዝግጅቱን ማጠናቀቁን ገልጿል፡፡ በ
ቅርቡ በአዲስ አበባና በኦሮሚያ ክልል ሁለት ቅርንጫፎቹን በመክፈት የቅርንጫፍ ቢሮዎቹን ቁጥር ወደ 15 ከፍ ለማድረግ ማቀዱንም ኃላፊዎቹ ገልፀዋል፡፡

Read 1688 times
Administrator

Latest from Administrator