Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Friday, 06 January 2012 09:37

ጐንደር ለሁለተኛ ጊዜ የጥምቀት ካርኒቫል ታከብራለች

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ከ16ኛው እስከ 20ኛው ክፍለ ዘመን መዳረሻ የኢትዮጵያ ዋና ከተማ የነበረችውና በጥምቀት በዓል አከባበሯ በመላ ኢትዮጵያና በመላ ዓለም የምትታወቀው ጐንደር ዘንድሮ ለሁለተኛ ጊዜ የጥምቀት ካርኒቫል ታከብራለች፡፡ ጥምቀትን በመንተራስ የሚከበረው ካርኒቫል በጐንደር ከተማ ከጥር 9 እስከ 13 ቀን 2004 ዓ.ም በተለያዩ ዝግጅቶች ይከበራል፡፡ ከተማይቱን የሚጐበኙ የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገራት ጐብኚዎችን ቁጥር ለማበራከት የተሻለ አገልግሎት ይሰጥበታል ተብሎየታለመውን ዝግጅት ከከተማዋ ባህልና ቱሪዝም ፅህፈት ቤት ጋር በመሆንየሚያስተባብረውሀገሬሚዲያናኮሙኒኬሽንእንደሆነ ታውቋል፡፡

“ኢትዮጵያን በጐንደር ብሔራዊ ካርኒቫል” በሚል ርእስ በሚቀርበው ዝግጅት የከተማዋ አስተዳደርየጐብኚዎችንቆይታ በማራዘም የኢትዮጵያን ጥሩ ገፅታ ለማስተዋወቅና የቱሪዝም ፍሰቱን ለመጨመር ያቀደ ሲሆን ዓመቱን ሙሉ ቅስቀሳ መደረጉንም አስታውቋል፡፡ 150ሺ የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገራት ጐብኚዎች ከከተማው ነዋሪ ጋር ይታደሙበታል ተብሎ የሚጠበቀውዝግጅት፤ በታሪካዊ ቅርሶችና ትውፊቶች ታጅቦ ይቀርባል ተብሏል፡፡ ዝግጅቶቹ መሃል በኦርቶዶክሳዊ ሥርዓት በወጣቶች የሚቀርብ የቅኔ፣ የአቋቋምና ዜማ፣ የፈረስ ጉግሥና ሠረገላ ትርዒት፣ ነጋሪት ጉሰማ እና እምቢልታ መንፋት፤ በፋሲል ግንብ ውስጥ የባህላዊ ዘፈን ትርዒት እንዲሁም በዳግማዊ አፄ ቴዎድሮስ ጊዜ ተካሂዶ የነበረውን የቁንጅና ውድድር የሚዘክር ታሪካዊ ተውኔትና የቁንጅና ውድድር፤ ይገኙበታል፡፡

 

 

 

Read 2354 times Last modified on Friday, 06 January 2012 09:41