Saturday, 15 November 2014 12:00

“ለራስ ማን እንደራስ” መፅሃፍ ይመረቃል

Written by 
Rate this item
(4 votes)

በዶ/ር ወሮታው በዛብህ የተዘጋጀውና ከ70 የሚበልጡ ሥራ ፈጣሪዎችን ታሪክ የሚያስቃኘው “ለራስ ማን እንደራስ” የተሰኘ መጽሀፍ ሰሞኑን ለንባብ የበቃ ሲሆን የፊታችን ረቡዕ ከቀኑ 10 ሰዓት ጀምሮ በአምባ ሆቴል ይመረቃል፡፡ መፅሀፉ በራስ ፈጠራ እንዴት መለወጥ እንደሚቻልና በመፅሀፉ የተካተቱ ከ70 በላይ ሰዎች እንዴት እንደተለወጡ የተርካል ተብሏል፡፡ በምረቃው ዕለት የጂኒየስ ማሰልጠኛ ተቋም ሰልጣኞች ምረቃ፣ የስኬታማ ሰዎች ልምድና ሌሎች ፕሮግራሞች እንደሚካሄዱ ተጠቁሟል፡፡ መፅሀፉ በ60 ብር ለገበያ የቀረበ ሲሆን የመፅሀፉ አዘጋጅ በሥራ ፈጠራና ብልፅግና ዙሪያ በርካታ መፃህፍትን ለንባብ ማብቃታቸው ይታወቃል፡፡

Read 2539 times