ጉርድ ሾላ አካባቢ የሚገኘው የሉሲ አካዳሚ ተማሪዎች ገናን (የልደት በዐልን) አርብ እለት በመፃህፍት ስጦታ አከበሩ፡፡ በእለቱ በተከናወነ የመፃህፍት ንባብና የግጥም ውድድር ላሸነፉና በትምህርታቸው ብልጫ ላስመዘገቡ ተማሪዎች ለገና ሥጦታ የተረት መፃህፍት ተበርክተውላቸዋል፡፡ ከጀርመን የባህል ተቋም ጋር በመተባበር በቀረበው ዝግጅት ከ5-12 ዓመት ያሉ ህፃናት ታድመውታል፡፡ ይህ በዚህ እንዳለ የትምህርት ቤቱ ተማሪዎች የመማርያ ቁሳቁስ እና ልብሶች ለሜሪ ጆይ በእርዳታ ሰጥተዋል፡፡ ረቡዕ ጧት በትምህርት ቤቱ ቅፅር ግቢ በተከናወነ ሥነ ሥርዓት የሜሪጆይ ሥራ አስኪያጅ ሲስተር ዘቢደር ዘውዴ ከአርቲስት አብራር አብዶ እና አርቲስት ትዕግስት ግርማ ጋር በመሆን እርዳታውን ተረክበዋል፡፡